Get Mystery Box with random crypto!

የአብክመ ፍትሕ ቢሮ ANRS JUSTICE BUREAU

टेलीग्राम चैनल का लोगो amharaattorney — የአብክመ ፍትሕ ቢሮ ANRS JUSTICE BUREAU
टेलीग्राम चैनल का लोगो amharaattorney — የአብክመ ፍትሕ ቢሮ ANRS JUSTICE BUREAU
चैनल का पता: @amharaattorney
श्रेणियाँ: राजनीति
भाषा: हिंदी
ग्राहकों: 2.34K

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


नवीनतम संदेश 6

2023-04-08 03:17:28
በጃዊ ወረዳ በካቫ አቦ ት/ቤት ለሚገኙ ተማሬዎች ለወ=563 ለሴት=642 በድምር።1205 ለሚሆኑ ተማሬዎች በጎጅ ልማዳዊ ድርጊቶ በተለይም ያለእድሜ ጋብቻ፣ በሴቶች ህፃናት ላይ የሚደረስ የሐይል ጥቃት ፣አሥገድዶ መደፈር እና ሌሎች የተማሬዎችን ሥነ-ምግባር በተመለከተ በቀን 27/07/2015 ዓ.ም የወረዳ ሴቶች ጉዳይ ባሉበት በተቀናጄ ሁኔታ ትምህርቱ ተሠጥቷል።
45 viewsAlemshet Miheretie, 00:17
ओपन / कमेंट
2023-04-08 03:16:26 በ2014 ዓ.ም በነበረዉ አጠቃላይ የስራ አፈጻጸም የ 24 ወረዳ /ንኡስ ወረዳዎች አፈጻጸማቸዉ በመምሪያ የደረጃ ኮሚቴ ተቋቁሞ የተለያዩ ስራን መሠረት ያደረጉ መስፈርቶች በማዘጋጀት
የወረዳወችን ደረጃ አዉጥቷል።
በዚህም መሠረት
1_ጎንደር ከተማ አስ ፍትህ ጽ/ቤት
2_ምዕራብ ደንቢያ ወረዳ ፍትህ ጽ/ቤት
3_ጎንደር ዙሪያ ወረዳ ፍትህ ጽ/ቤት

ሲሆኑ በተለያዩ ምክንያቶች የዘገየ ቢሆንም የምስጋና የምስክር ወረቀት
መጋቢት 27/2015 ከ9 ወር ግምገማ በኋላ በመምሪያዉ ኃላፊ ተሰጥቷቸዋል::
43 viewsAlemshet Miheretie, 00:16
ओपन / कमेंट
2023-04-07 14:27:12
286 viewsAlemshet Miheretie, 11:27
ओपन / कमेंट
2023-04-07 14:18:36
293 viewsAlemshet Miheretie, 11:18
ओपन / कमेंट
2023-04-07 11:46:49 በስራ ተግባር የሚፈፀም የመዉሰድና የመሰወር የሙስና ወንጀል የተከሰሱት ግለሰቦች ተቀጡ፡፡
1ኛ. ተከሳሽ ሳጅን መላኩ ምህረት የ5ኛ ሻለቃ የ3ኛ ሻንበል አዛዥ፣2ኛ ተከሳሽ የ5ኛ ሻለቃ የ3ኛ ሻንበል አስተዳደር 3ኛ. ተከሳሽ የ5ኛ ሻለቃ ምክትል አዛዥ በአብክመ ልዩ ኃይል ፖሊስ ተከዜ ክፍለ ጦር ሁነዉ ሲሰሩ የነበሩ ግለሰቦች በኢ.ፌ.ዲ.ሪ የወንጀል ህግ አንቀፅ 32/1/ሀ/፣የሙስና ወንጀሎችን ለመደንገግ የወጣዉን አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀፅ 15(1)(ለ) እና (3)ን በመተላለፍ የማይገባቸዉን ቁሳዊ ጥቅም ለራሳቸዉ ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰዉ ለማስገኘት በማሰብ ሚያዚያ 28 ቀን 2014 ዓ/ም በግምት ከቀኑ 8፡00 ስዓት በሚሆንበት ጊዜ በሰሜን ጎንደር ዞን ጃናሞራ ወረዳ አይጥ ጀሮ ከሚባል ስፍራ የተከዜ ክፍለ ጦር የ5ኛ ሻለቃ የ3ኛ ሻንበል የልዩ ሃይል ፖሊስ አባላት በህግ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 2,304,000/ሁለት ሚሊዮን ሶስት መቶ አራት ሽህ / ብር ከእነ ተጠርጣሪዎቹ ይዘዉ ለተከሳሾች አስረክበዋቸዉ ተከሳሾች ገንዘቡን ከተረከቡ በኋላ ገንዘቡን ሲያዘዋዉሩ የነበሩትን ግለሰቦች በአካባቢዉ በነበረዉ የልዩ ሃይል ካምፕ ለ2 ቀን አስረዉ ከቆዩ በኋለ ከተያዘዉ ገንዘብ ዉስጥ ለዐቃቤ ህግ ምስክር ለሆነዉ ግለሰብ 350,000/ሶስት መቶ ሃምሳ ሽህ /ብር በመመለስ ግለሰቦችን ፈትተዉ ከለቀቁ በኋላ ቀሪዉ ገንዘብ 3ኛ ተከሳሽ ወደ አለበት ካምፕ በመዉሰድ ገንዘቡ በህጋዊ መንገድ ወደ ሚመለከተዉ አካል ቀርቦ መቀመጥ እያለበት ተከሳሾች በመመሳጠር በአደራ የተረከቡትን ጥሬ ገንዘብ ከፊሉን የሰወሩት ከፊሉን ደግሞ የተከፋፈሉት በመሆኑ በፈፀመት በስራ ተግባር የሚፈፀም የመዉሰድና የመሰወር የሙስና ወንጀል ተከሰዋል፡፡
ስለሆነም የጃናሞራ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት የሙስና ወንጀል ምርመራ ክፍል አጣርቶ የላከውን መዝገብ የሰሜን ጎንደር ዞን ፍትህ መምሪያ የሙስና ወንጀል ጉዳዮች የስራ ሂደት ክስ መስርቶበት የሰሜን ጎንደር ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲያከራከር ከቆየ በኋላ ተከሳሾች በመከላከያ ምስክሮች ክሱን ማስተባበል ባለመቻላቸዉ ፍርድ ቤቱ መጋቢት 28/2015 ዓ/ም በዋለዉ ችሎት ተከሳሾችን ያስተምራል፤ሌሎችንም ያስጠነቅቃል ያለዉን ለእያንዳንዳቸዉ የ9 ዓመት ፅኑ እስራት እና 3,000/ሶስት ሽህ ብር ቅጣት ወስኖባቸዋል፡፡
347 viewsAlemshet Miheretie, 08:46
ओपन / कमेंट
2023-04-07 10:52:45 አሸናፊ ሞሱ የተባለ ግለሰብ በምስራቅ ጎጃም ዞን አዋበል ወረዳ ወጀል ከተማ ላይ መደበኛ የመኖሪያ ቦታውን በማድረግ ከተቀመጠ በኋላ ለተለያዩ ግለሰቦች የትምህርት ማስረጃ፣ፓስፖርት፣የህክምና ማስረጃ እና መንጃ ፈቃድ በሀሰት እየሰራ ይሸጣል በሚል ለፖሊስ በደረሰ ጥቆማ መሰረት የወረዳው ፖሊስ ጽ/ቤት የወንጀል ምርመራ ክፍል ወደ ግለሰቡ የመኖሪያ ቤት በመሄድ በቁጥጥር ስር አውሎ ብርበራ ሲያደርግ ተሰርተው የተቀመጡ የተለያዩ ሀሰተኛ ሰነዶች፤ለዚሁ ተግባር የሚያገለግሉ አንድ ላፕቶፕና አንድ ዴስክቶፕ እንዲሁም ቀለሞችንና ወረቀቶችን ያገኘ በመሆኑ ምርመራ አጣርቶ መዝገቡን ለምስራቅ ጎጃም ዞን ፍትህ መምሪያ የሙስና ወንጀል ጉዳዮች የስራ ሂደት ልኮታል፡፡የምርመራ መዝገቡ የደረሰው የዞኑ ፍትህ መምሪያ የስራ ሂደትም በተጠርጣሪው ላይ የሙስና ወንጀሎችን ለመደንገግ በወጣው አዋጅ አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀጽ 23/1 ን በመጥቀስ ክስ መስርቶበታል፡፡የምስራቅ ጎጃም ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በቀረበው ክስ ላይ ሲያከራክር እና በምርመራ መዝገቡ የተያያዙ የሰነድ ማስረጃዎችን ሲመረምር ከቆየ በኋላ የተከሰሰበትን የወንጀል ድርጊት ስለመፈጸሙ ያረጋገጠ በመሆኑ ጥፋተኛ በማለት በ8 ዓመት ጽኑ እስራት እና በ5000 /አምስት ሽህ/ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጣ፤በኤግዚቪትነት የተያዙትን ላፕቶፕና ዴስክቶፕ ለመንግስት ገቢ እንዲሆኑ በማለት ውሳኔ ሰጥቷል፡፡በመጨረሻም የምስራቅ ጎጃም ዞን ፍትህ መምሪያ የሙስና ወንጀል ጉዳዮች የስራ ሂደት መሪ አቶ ያለለት ሙኔ ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት ሲባል የሚዘጋጁ የሀሰተኛ ማስረጃዎች በሕዝብና በሀገር ላይ የሚያደርሱት ኪሳራ እጅግ ከፍተኛ ከመሆኑም በላይ ለህይወት መጥፋትም ዋነኛ ምክንያቶች በመሆናቸው የፍትህ ተቋማት በቅንጅትና በትብብር ትኩረት ሰጥተው በመስራት፤ህብረተሰቡም ጥቆማ በመስጠት በወንጀል ድርጊቱ የተሰማሩ ግለሰቦችን ወደ ህግ ማቅረብ ይገባል ብለዋል፡፡
327 viewsAlemshet Miheretie, 07:52
ओपन / कमेंट
2023-04-06 22:00:48 የማእከላዊ ጎንደር ዞን ፍትህ መምርያ የ2015 ዓ/ም    የ9 ወር እቅድ ክንውን የስራ አፈፃፀም ገመገመ
     ፍትህ መምርያው በስሩ የሚገኙትን 24 የወረዳ እና ንኡስ ወረዳ ፍትህ ጽ/ቤት ኃላፊዎች እና የዞን የስራ ሒደት አስተባባሪዎች እና ባለመያዎች እንዲሁም የጎንደር ከተማ አስተዳደር ፓሊስ መምርያ እናየጣቢያ የምርመራ ክፍል ኃላፊ የተከሳሽ እና ምስክር አቀራረብ በተጨማሪ የማእከላዊ ጎንደር ዞን የምርመራ ክፍል ኃላፊ ፣ ተከሳሽ እና ምስክር አቀራረብ በተገኙበት በ27/7/2015ዓ/ም የአንድ ቀን ግምገማ ያካሔደ ሲሆን ከሰአት በፊት የመምርያውን እና የወረዳዎችን የ9 ወር አፈፃፀም ገምግሟል ከሰአት በኋላ ደግሞ የተከሳሽ እና ምስክር አቀራረብ ፣ የምርመራ ጥራት፣የ38/ሐ/ አተገባበረ ፣ ውስብስብ እና ከባድ ወንጀሎቾ የፓሊስ እና ዐቃቤ ሕግ የትብብር ፣ስራን መሰረት ያደረገ ጤናማ ግንኙነት ዙርያ መነሻ ያደረገ ግምገማ ተካሔዷል በግምገማው በጥንካሬ ከታዩት በወረዳ ደረጃ በፍታብሔር እና በወንጀል ብልሹ አሰራርን በመታገል የላቀ እንቅስቃሴ መኖሩን፣ ከፓሊስ ጋር በመተባበር በተከሳሽ እና ምስክር አቀራረብ ዙርያ የተዘጉ መዛግብት ማንቀሳቀስ፣ በሙስና ወንጀል ጉዳይ ለረጅም ጊዜ ለተጨማሪ ምርመራ የተላኩ መዛግብትን ተሟልተው እንዲመለሱ የተሰሩ ስራ ዎች በጥንካራ ከተገመገሙት ጥቂቶቹ ሲሆኑ በድክመት ደግሞ በተከሳሽ እና ምስክር አቀራረብ ዙርያ ተቆራርጦ አለመስራት ከዚህ ጋር በተያያዘ ከፓሊስም ሆነ ከዐቃቤ ሕግ የሚታይ የስነምግባር ችግር መኖሩ፣ የምርመራ ስራ የጥራት መጓል፣የሙስና መዛግብትን በሚመለከት በአንዳንድ ወረዳዎች ተቆራረጦ አለመስራት ፣ በጠለፋ እና በሕገወጥ የሰዎች ዝውውር እንዲሁም የጦር መሳርያ ዝውውር ላይ ሕገወጦችን በቀላሉ በዋስ መልቀቅ እና በአጠቃላይ የስነምግባር ችግር መታየት ዐቃቢያነ ሕግ በዞን ደረጃ በተለይ የልዩልዩ ወንጀል ጉዳይ የስራ ሒደት ወደችሎት ሲገባ በቂ ዝግጅት አድርጎ ጠንካራ ክርክር አለማደረግ ላይ ችግር ያለባቸው ባለሙያዎች መኖር በድክመት ከተገመገሙት ለአብነት የሚወሰዱ ናቸው በመጨረሻ በግምገማው የታዩትን ድክመቶች በማረም እና በጥንካሬ የተገመገሙትን ይበልጥ በማጠናከር ከፓሊስ ተቋማት ጋር ተባብሮ በመስራት የቀሪ 3 ወራት አፈፃፀምን ወጤታማ ለማደረግ የጋራ መግባባት ተደርሶ የለቱ ግምገማ ተጠናቋል።
393 viewsAlemshet Miheretie, 19:00
ओपन / कमेंट
2023-04-05 20:07:11 "የአማራ ሕዝብ ሕግና የፍትሕ ሥርዓት እንዲሰፍን የሚፈልግ፤ ለሕግና ሥርዓትም ቀናኤ የኾነ ሕዝብ ነው" የባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ ምሁራን

ባሕርዳር: መጋቢት 27/2015 ዓ.ም የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሕግ ትምህርት ቤት የአማራ ሕዝብ በኢፌዴሪ ሕገ-መንግሥት ላይ በሚያነሳቸው መሰረታዊ ጥያቄዎችና ፍላጎቶች ላይ ያተከረ ከባለድርሻ አካላት ጋር ተከታታይ ውይይቶችን ሲያደርግ መቆየቱን አስታውቋል።

ውይይቱ ከዓቃቢያነ ሕጎች ፣ከዳኞች ፣ከጠበቆችና ከዩኒቨርሲቲው የሕግ ምሁራን ጋር ነው ሲካሄድ የቆየው።

ዩኒቨርሲቲው ከውይይቱ የተገኙ ግብዓቶችንና የጥናት ውጤቶችን ለባለድርሻ አካላት ሪፖርት አቅርቧል።
በመድረኩ የተገኙት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት እሰይ ከበደ (ዶ.ር) በሥራ ላይ ያለው የኢፌዴሪ ሕገ-መንግሥት ከአማራ ሕዝብ ጥቅምና ፍላጎት አንጻር ብሎም በሀገራዊ ግንባታው ጠቃሚ ግብዓት ለመስጠት ነው የሕግ ትምህርት ቤቱ ምሁራን ከአጋር አካላት ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶችን ያካሄዱት ብለዋል።

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሕግ ትምህርት ቤት ጥናትን መሰረት ያደረገ በሀገር መሰረታዊ ውቅር ከፍተኛ ፋይዳ ያላቸው ጉዳዮች ላይ የላቀ አበርክቶ እያረገ እንደኾነም ምክትል ፕሬዚዳንቱ ተናግረዋል።

የአማራ ሕዝብ ሕግና የፍትሕ ሥርዓት እንዲሰፍን የሚፈልግ፣ለሕግና ሥርዓትም ቀናኤ የኾነ ሕዝብ ነው ያሉት ዶክተር እሰይ አሁን በሥራ ላይ ባለው በኢፌዴሪ ሕገ- መንግስት ከመብትና ማንነት፣ከልማት ተጠቃሚነት እስከ ፍላጎቱና ጥቅሙን የሚያስከበርለት የሕግ ሥርዓት እንዳልተዘረጋለት ያምናል ብለዋል።

የአማራ ሕዝብ የጸጥታና የደኅንነት ጉዳይ በዙሪያው የሚደርስበት ትንኮሳ እርፍት እየነሳው፣ ባልተመለሱለት የማንነት ጥያቄዎችም የሚዋከብ ሕዝብ ኾኗል ብለዋል።

በውይይት መድረኩ በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሕግ ትምህርት ቤት መምህር ተመስገን ሲሳይ የኢፌዴሪ ሕገ-መንግሥት ከጅምሩ የረቀቀበት ፣የጸደቀበት አጠቃላይ ሁኔታና አሁን የሚነሳበት የቅቡልነት ጥያቄ ላይ ያተኮረ የጥናት ሪፖርት አቅርበዋል።

የሕግ መምህሩ ተመስገን ሲሳይ እንዳሉት ማንነትን መሰረት አድርጎ የተመሰረተው የኢፌዴሪ ሕገ-መንግሥት የአማራን ሕዝብ በማንነቱ በሚገባ ያልወከለና ያላሳተፈ ነው ብለዋል።

ዛሬ ላይ በየሁኔታው እንደ ሕዝብ የሚደርስበት ወከባም በልኩ የሚወክለውና መብትና ጥቅሙን የሚያስከብርለት ሕገ- መንግሥት ያለመኖር ውጤት ነው ሲሉ አብራርተዋል።

ሕገ- መንግሥቱ ሲረቀቅም ኾነ ሲጸድቅ አማራን በሚገባ የሚወክል ፣ፍላጎቱንና ጥቅሙን የሚያስከብር ተወካይ እንዳልነበረው ባቀረቡት የጥናት ሪፖርት አመላክተዋል። እንዲህ አይነት ውይይቶች የአማራ ሕዝብ ለምን የሕገ-መንግሥቱን መሻሻል ይፈልጋል፣ እንዴትስ እንዲሻሻል ይፈልጋል የሚሉ ነጥቦችን በዕውቀት ላይ ተመስርቶ ለማቅረብ እንደሚረዳም ተናግረዋል።

በመድረኩ የሕገ-መንግሥት ማሻሻያ (ለውጥ) እንዲደረግ ግድ የሚሉ ጉዳዮችና ማሻሻል ሥራው ሊተኮርባቸው የሚገባቸው ነጥቦች ላይ ያተኮረ የጥናት ሪፖርት ቀርቦ ውይይት እንደሚደረግበት ከመርሐ ግብሩ መረዳት ተችሏል።

የመንግሥት የሥራ ኀላፊዎች እና ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበት የዛሬው የውይይት መድረክ የጥናት ሪፖርቱን ተደራሽ ለማድረግ ፣ለማዳበርና በቀጣይ አቅጣጫዎችን በጋራ ለማስቀመጥ የሚያስችል ነው ተብሏል።
አሚኮ
793 viewsAlemshet Miheretie, 17:07
ओपन / कमेंट
2023-04-05 20:06:59
559 viewsAlemshet Miheretie, 17:06
ओपन / कमेंट
2023-04-03 21:23:17 ከሳሽ .......የጠ/ዐ/ህግ
ተከሳሽ .....ደስታው ጥላሁን አባይ አድራሻ ...ዳባት ወረዳ አጅሬ ቀበሌ
ተከሳሹ ካልተያዘ ግብረ አበሩ ጋር በመሆን ጥቅምት 2 ቀን 2014 ዓ/ም በጠገዴ ወረዳ ሸኒ ቀበሌ ልዩ ስሙ ፈንጥሮ በርሃ ላይ የግል ተበዳይ የሆኑትን 1ኛ ፈረንጁ አየነው 2ኛ አዲሱ ገብሬ አዝመራና ከብት እየጠበቁ እያለ ካልተያዘው ግብረ አበሩ ጋር በመሆን በያዘው ሰደፍ ክላሽ በማንገራገር እንዲሁም ከቤተሠብ ብር አስመጣ እያለ በመደብደብ ከፍተኛ እንግልት ሲያደርስባቸው ቆይቶ ጥቅምት 16 ቀን 2014 ዓ/ም ከምሽቱ 3:00 ሲሆን ሸኒ ቀበሌ አናሴ የተባለች ጎጥ ላይ 250000(ሁለት መቶ አምሳ ሽ) ብር ተቀብሎ ከ13 የእንግልት ቀናት በኋላ የግል ተበዳይን የለቀቃቸው ሲሆን የጸጥታ ሀይሉ ጠላፊውን ወደ ህግ ያቀረበ በመሆኑ የጠ/ወ/ ፍ/ጽ/ ቤት የወንጀል የስራ ሂደት ተጠርጣሪው ላይ የወንጀል ህግ አንቀጽ ቁጥር 290/1/(ሀ) እና /2/ (ሐ) ጠቅሶ ክስ ያቀረበ ሲሆን ተጠርጣሪው ክዶ የተከራከረ በመሆኑ አቃቤ ህግ ምስክሮችን አሰምቶ ፍርድ ቤት የተከላከል ብይን ሰጥቷል ተጠርጣሪው 6 የመከላከያ ምስክር አቅርቦ ያሰማ ቢሆንም መከላከል ባለመቻሉ የጠገዴ ወረዳ ፍርድ ቤት በቀን 18/07/2015 ዓ/ም በዋለው ችሎት ተከሳሹን ያርማል ሌሎችንም ያስተምራል ያለውን 13 ዓመት ፅኑ እስራት ወስኖበታል
   የጠገዴ ወረዳ ፍ/ጽ/ቤት
257 viewsAlemshet Miheretie, 18:23
ओपन / कमेंट