2022-05-04 21:11:00
የኢፌዲሪ ፍትሕ ሚኒስቴር ከክልል እና ከተማ አስተዳደር ፍትሕ ቢሮዎች ጋር ወጥ የሆነና የተደራጀ ሪፓርት ለማቅረብ በአዲሱ የሪፓርት ማቀረቢያ ቅፅ ዙሪያ የዙም ውይይት አካሄደ። ሚያዚያ 26 ቀን 2014.
የተጠቃለለ፣ወጥ የሆነ እና በተደራጀ መንገድ የኢፌዲሪ ፍትሕ ሚኒስቴር እና የክልል እና የከተማ ፍትሕ ቢሮዎች ዐቃቤ ሕግ የተሰጠውን ተልዕኮ፣ ተግባርና ኃላፊነት ውጤታማ በሆነ መልኩ መፈፀም እንዲቻል በስራ ክፍሎች የሚከናወኑ ተግባራት ሪፓርት አቀራረብ ወጥነት ያላቸው ተነባቢ፣ ግልፅና ተጠያቂነት በተሞላበት መልኩ ለማቅረብ ዓላማ ይዞ የሚከናውን መሆኑ በውይይቱ ተገልዷል።
በቀጣይ የክልል እና የከተማ አስተዳደር ፍትሕ ቢሮዎች አዲሱን የሪፓርት ፎርማት ጠንቅቀው በመረዳት ውጥነት ባለው መንገድ ሪፓርት ሊያደርጉ እንደሚገባ በውይይቱ ተነስቷል።
በቀጣይ ከዙም ውይይቱ በመነሣት በሪፓርት አላላኩ ላይ ተጨማሪ የግንዛቤ እና የመወያያ መድረክ በመፍጠር የዳይሬከተሮች እና የባለሙያዎችን ግንዛቤ በማሳደግ ወጥ እና አዳጊ የሪፓርት አቀራረብ እንዲኖር ማድረግ ይገባል ተብሏል።
252 viewsAlemshet, edited 18:11