Get Mystery Box with random crypto!

የአብክመ ፍትሕ ቢሮ ANRS JUSTICE BUREAU

टेलीग्राम चैनल का लोगो amharaattorney — የአብክመ ፍትሕ ቢሮ ANRS JUSTICE BUREAU
टेलीग्राम चैनल का लोगो amharaattorney — የአብክመ ፍትሕ ቢሮ ANRS JUSTICE BUREAU
चैनल का पता: @amharaattorney
श्रेणियाँ: राजनीति
भाषा: हिंदी
ग्राहकों: 2.34K

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


नवीनतम संदेश 59

2022-06-12 05:11:27
በኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን በጂሌ ጥሙጋ ወረዳ በዩ.ኤን.ዲ.ፒ(UNDP) የበጀት ድጋፍ በወረዳው ውስጥ በሴቶች እና ህፃናት ላይ የሚፈፀሙ የኃይል ጥቃቶችን በሚመለከት ለጥቃቱ ተጋላጭ ለሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እየተሠጠ ይገኛል::

የስልጠናው ተሳታፊዎች
1.ከቀበሌ የሴቶች አደረጃጃት ፣ከሴቶች ማህበር፣ከሴቶች ሊግ እና ከሴቶች ፌዴሬሽን
2.ከህፃናት ፓርላማ
3.ከ3ቱ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች የልጃገረድ ክበባት
4.ከሁለት የበጎ አድራጎት ማህበራት
5.አካል ጉዳተኞች የተውጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ናቸው::
111 viewsAlemshet, edited  02:11
ओपन / कमेंट
2022-06-12 05:03:01
በምዕራብ ጎጃም ዞን የፍኖተ ሠላም ማረሚያ ቤት የሚነኙ የህግ ታራሚዎችን እና የጊዜ ቀጠሮ እስረኞችን የሠብዓዊ መብት አያያዝ እና ልዮ ልዮ አቤቱታዎች መፍትሔ እና ምላሽ ለመስጠት ያለመ ጉብኝት የዞኑ ፍትህ መምሪያ ከዞን ፖሊስ ፣ የወረዳ ዐቃቢ ህግ ዳኞች እና መርማሪ ፖሊሶች ጋር በመቀናጀት ዛሬ ሠኔ 4 ቀን 2014 ዓ ም የተከናወነ ሲሆን በጉብኝቱ ታራሚዎች ልዮ ልዩ አቤቱታዎችን አቅርበው ምላሽ እና ማብራሪያ ተሰጥቷል። በተለይም የጊዜ ቀጠሮ እስረኞች ክስ ሳይቀርብብን ረዘም ላለ ጊዜ ታስረናል ሲሉ ያቀረቡትን አቤቱታ በተመለከተ የምርመራ መዝገቦች ከፖሊስ ያልተላኩት በአጭር ጊዜ ቀሪ ስራዎች ተጠናቀው ለዐቃቤ ህግ እንዲቀርቡ ለዐቃቢ ህግ የቀረቡ መዝገቦችን በአጠረ ጊዜ ውሳኔ እንዲያገኙ ትኩረት ተሠጥቶ እንደሚሠራ የፍትህ መምሪያው የልዮ ልዮ ወንጀል ጉዳዮች አስተባባሪ አቶ ገደፋው ያለው ማብራሪያ ሠጥተዋል። በጉብኝቱ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ፖሊስ ዐቃቢ ህግ እና ዳኞች በተገኙበት በቅንጅት መደረጉ ለየችግሮቹ ባለቤት ሠጥቶ ለመፍትሔው መስራት ስለሚያስችል ተጠክሮ መቀጠል እንዳለበትም የፍትህ መምሪያው የሙስና ወንጀል ጉዳዮች አስተባባሪ አቶ እሱባለው መኮንን ገልጸዋል።
138 viewsAlemshet, edited  02:03
ओपन / कमेंट
2022-06-11 02:19:27
ዮ ኤስ ኤ አይ ዲ ፍትሕ ተግባራት በኢትዮጵያ የገንዘብ ድጋፍ ከአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ ጋር በመተባበር እሁድ ሰኔ 5 ቀን 2014ዓ.ም ከምሽቱ 2:30 ሰዓት ጀምሮ በ"ፍትሕ" የቴሌቪዥን ኘሮግራማችን የውክልና ሕግን በተመለከተ የአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ የክልል ዐቃቤ ሕግ የሆኑት አቶ ዘላለም ከፋለ እና ወ/ሮ ናርዶስ ጥላሁን በአሚኮ ቴሌቪዥን ቀርበው ማብራሪያ ይሰጣሉ።አዳምጠው ተመልክተው አስተያየት ይስጡን?
182 viewsAlemshet, edited  23:19
ओपन / कमेंट
2022-06-10 19:40:20
ዮ ኤስ ኤ አይ ዲ ፍትሕ ተግባራት በኢትዮጵያ የገንዘብ ድጋፍ ከአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ ጋር በመተባበር እሁድ ሰኔ 5 ቀን 2014ዓ.ም ከምሽቱ 2:30 ሰዓት ጀምሮ በ"ፍትሕ" የቴሌቪዥን ኘሮግራማችን የውክልና ሕግን በተመለከተ የአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ የክልል ዐቃቤ ሕግ የሆኑት አቶ ዘላለም ከፋለ እና ወ/ሮ ናርዶስ ጥላሁን በአሚኮ ቴሌቪዥን ቀርበው ማብራሪያ ይሰጣሉ።አዳምጠው ተመልክተው አስተያየት ይስጡን?
118 viewsAlemshet, edited  16:40
ओपन / कमेंट
2022-06-10 16:54:48
የብርጋዴር ጀኔራል ተፈራ ማሞ የዋስትና ይፈቀድልኝ ጥያቄ እና የፍርድ ቤቱ ውሳኔ
(ሰኔ 03/2014 ዓ/ም)ብርጋዴር ጀኔራል ተፈራ ማሞ ተጠርጥረው በፖሊስ ቁጥጥር ስር ከዋሉ ጊዜ ጀምሮ ክስ ሳይቀርብባቸው በጊዜ ቀጠሮ ቆይተው ሰኔ 02/2014 ዓ.ም በዋለው ችሎት መርማሪ ፖሊስ ምርመራውን አጠናቅቄ የተጣራውን የምርመራ መዝገብ ለዐቃቤ ሕግ ለመላክ በዝግጅት ላይ ነኝ ያለ ሲሆን የክልሉ ፍትሕ ቢሮ ዐቃቤ ሕግ ምርመራው ተጠናቋል፤የክስ መመስረቻ ጊዜ 15 ቀን ይሰጠኝ ሲል ለፍርድ ቤቱ አመልክቷል፡፡
የተጠርጣሪው ጠበቆች በበኩላቸው ምርመራው ከተጠናቀቀ ደንበኛችን የተጠረጠሩበት የወንጀል ድርጊት ዋስትና የሚያስከለክል ባለመሆኑና ሊጠፉ የማይችሉ ታዋቂ ሰው በመሆናቸው ዋስትናቸው ሊከበርላቸው ይገባል ሲሉ ተከራክረዋል፡፡
ፍርድ ቤቱም ምርመራው የተጠናቀቀ በመሆኑ የጊዜ ቀጠሮውን ጉዳይ ዘግቶ የተጠርጣሪ ጠበቆች ባቀረቡት የዋስትና ጥያቄ ላይ ዐቃቤ ሕግ አስተያየት እንዲሰጥበት አድርጓል፡፡
ዐቃቤ ሕግም ተጠርጣሪው የተጠረጠሩት በሽብር ወንጀል ስለሆነ እና በሌሎች ተጨማሪ የወንጀል አይነቶች ስለሆነ ሊቀርቡ ስለማይችሉ ዋስትና ሊፈቀድላቸው አይገባም ሲል ተከራክሯል፡፡
ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኙን ክርክር ሰምቶ በዋስትና ጥያቄው ላይ ብይን ለመስጠት ለሰኔ 3/2014 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ቀጠሮ መስጠቱ ይታወቃል።
ፍርድ ቤቱም በያዘው ቀጠሮ መሰረት መዝገቡን መርምሮ ዐቃቤ ሕግ ዋስትናው እንዲከለክል ያቀረባችውን ምክንያቶች ባለመቀበል ለተጠርጣሪው በ30,000 /ሰላሳ ሺህ/ ብር ዋስትናውን ፈቅዷል፡፡
225 viewsAlemshet, edited  13:54
ओपन / कमेंट
2022-06-09 21:43:14

828 viewsAlemshet, 18:43
ओपन / कमेंट
2022-06-09 21:38:00
ዮ ኤስ ኤ አይ ዲ ፍትሕ ተግባራት በኢትዮጵያ የገንዘብ ድጋፍ ከአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ ጋር በመተባበር እሁድ ሰኔ 5 ቀን 2014ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ሰዓት ጀምሮ በ"ፍትሕ" የሬዲዮ ኘሮግራማችን የኢንቨስትመንት አዋጁ ለባለሃብቶች የሚሰጠው ጥበቃና ከለላ ምን ይመስላል? የባለሃብቶች መብትና ግዴታዎች ምን ምን ናቸው? በሚል ጉዳይ የአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ የክልል ዐቃቤ ሕግ የሆኑት አቶ ዳኝነት ይግዛው በአማራ ሬዲዮ እና በኤፍኤም ጣቢያዎች ማብራሪያ ይሰጣሉ።አዳምጠው አስተያየት ይስጡን?
311 viewsAlemshet, edited  18:38
ओपन / कमेंट
2022-06-09 17:23:13 የ 14 አመት ህፃን ሴት ልጅ የጠለፈውና አስገድዶ የደፈረው ግለሰብ በ11 አመት ፅኑ እስራት ተቀጣ
ተከሳሽ ደረሰ ተክሌ የተባለው ግለሰብ በበረኸት ወረዳ 08 ቀበሌ ነዋሪ ሲሆን የ14 አመት ልጅ የሆነችውን ከምትኖርበት ቤት ከግብረ አበሩ ሻንበል አለማየሁ ጋር በመሆን በሀይል ሚያዚያ 28 ቀን 2014 ዓ.ም በመጥለፍ፣ጫካ ለጫካ እጇን በመጎተት ወደ 06 ቀበሌ ካመጣት ቡኃላ ከግለሰብ ቤት ውስጥ አስገብቶ አስገድዶ የደፈራት በመሆኑ ምርመራ ሲጣራ ቆይቶ የምርመራ መዝገቡ ለአቃቤ ህግ ፅ/ቤት ወንጀል ስራ ሂደት ተመርቶ የምርመራ መዝገቡን የተመለከተችው አቃቤ ህግም በ1ኛ ተከሳሽ ላይ ሴትን ልጅ አስገድዶ በመድፈር እና ሴትን ልጅ በሀይል በመጥለፍ እንዲሁም 2ኛ ተከሳሽን ደግሞ ለ1ኛ ተከሳሽ ጠለፋ ወንጀል በማገዝ ክስ በመመስረት ለወረዳው ፍርድ ቤት በማስገባት ተገቢው የህግ ሂደት ከተካሄደ ቡኃላ ተከሳሽ የአቃቤን ህግን ክስ መከላከል ባለመቻሉ ጥፋተኛ በማለት ግራ ቀኙ የቅጣት አስተያየት ሰጥተው ዛሬ በዋለው ችሎት ተከሳሾችን ያስተምራል ሌሎችም ከዚህ ቅጣት ይማራሉ ያለውን 1ኛ ተከሳሽ ደረሰ ተክሌ በ 11 አመት ፅኑ እስራትና 2ኛ ተከሳሽ ሻንበል አለማየሁን በ 1 አመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ አሳልፏል፡፡
የፍትህ ጽ/ቤቱ ኃላፊ የሆኑት አቶ ኤፍሬም አዳነ በበኩላቸው በሴት ልጅ ላይ የሚፈፀሙ ጥቃቶችን ሁሉም አካላት በጋራ መከላከል እንዳለበት አሳስበዋል:: "ፍትህ ለሁሉም!"
378 viewsAlemshet, 14:23
ओपन / कमेंट
2022-06-09 09:24:11
በደቡብ ወሎ ዞን በለገሂዳ ወረዳ ፍትሕ ጽ/ቤት እና ፍርድ ቤት በጋራ በመሆን በተቋሟቱ የአገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ የተደረገ የህዝብ የምክክር መድረክ
172 viewsAlemshet, edited  06:24
ओपन / कमेंट
2022-06-08 22:47:51 ከባድ የስርቆት ወንጀል የፈጸመው ግለሰብ በስምንት(8) አመት ከ5 (አምስት) ወር እስራት ተቀጣ
ከሳሽ የሰዴ ወረዳ ዓ/ህግ
ተከሳሽ አቶ ደሳለኝ ገብሬ ሙኔ የተባለው እድሜ 21፣ አድራሻ ሰዴ ወረዳ ሰዴ ከተማ ፣የትምህርት ደረጃ 10ኛ ክፍል፣የቤተሰብ ሁኔታ ያላገባ ፣ስራ ሽማ ስራ
የወንጀሉ ዝርዝር አፈጻፀም ተከሳሽ በ1996ዓ.ም ተደንግጎ የወጣውን የኢ.ፌዴ.ሪ የወንጀል ህግ አንቀጽ 669(3) ለ ላይ የተመለከተውን በመተላለፍ የማይገባውን ብልጽግና ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት በማሰብ ግንቦት 18 ቀን 2014ዓ.ም ከምሽቱ በግምት 4፡30 ሰዓት በሚሆንበት ጊዜ በሰዴ ወረዳ ሰዴ ከተማ ልየ ቦታው ቤተክርስቲያን መንደር እተባለ ከሚጠራው ቦታ ላይ የግል ተበዳይ ይልቃል ጫኔ ታሪኩን ቤት ምርግቱን ሰርስሮ በመገንጠልና በሩን ከፍቶ በመግባት የዋጋ ግምቱ 8000(ስምንት ሺህ )ብር የሆነአንድ ዩኒ ተች ስክሪን ስልክ ከ2 ሲም ካርድ ጋር ፣የዋጋ ግምቱ 900(ዘጠኝ መቶ )ብር የሆነ አንድ ትንሽ Jax ሞባይል ከሁለት ሲም ካርድ ጋር እና 3000(ሶስት ሺህ)ብር በድምሩ 11900(አስራ አንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ብር ሰርቆ በመውጣት በቀን 19/09/2014ዓ.ም ሰዴ ከተማ ልዩ ቦታው 4 ኪሎ እየተባለ ከሚጠራው ቦታ ላይ ከወሰዳቸው ስልኮችና ከ650 (ስድስት መቶ ሃምሳ ብር) ጋር የተያዘ በመሆኑ በፈጸመው ከባድ ስርቆት ወንጀል 5 የሰው ፣አንድ የሰነድ ማስረጃና የኢግዚቪት ማስረጃዎችን በማያያዝ የሰዴ ወረዳ ዓ/ህግ በቁጥር 698/14 በቀን 23/09/2014ዓ.ም ክስ መስርቷል፡፡
ክሱ የደረሰው የሰዴ ወረዳ ፍርድ ቤትም የተከሳሽን የእምነት ክህደት ቃሉን ሲጠየቅ የክስ ተቃውሞ የለኝም የወንጀል ድርጊቱን አልፈጸምኩም ጥፋተኛ አይደለሁም በማለት ክዶ በመከራከሩ ዓ/ህግ ይሰሙልኝ ያላቸውን ማስረጃዎች ሰምቷል፡፡በመቀጠል ተከሳሽ የቀረበበትን ክስ ሊከላከልና ሊያስተባብል ያልቻለ በመሆኑ የኢ.ፌዴ.ሪ የወንጀል ህግ አንቀጽ 669(3) ለ ላይ የተመለከተውን በመተላለፍ ከባድ ስርቆት ወንጀል ጥፋተኛ ነው በማለት በወ/መ/ስ/ስ/ህ/አንቀጽ 149(1) መሰረት ፍርድ ቤቱ የጥፋተኛነት ፍርድ ሰጥቷል፡፡
የሰዴ ወረዳ ፍርድ ቤት በቀን 01/10/2014ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሽ ከዚህ በፊት በመዝገብ ቁጥር 0200275 በቀን 11/10/2013ዓ.ም የኢ.ፌዴ.ሪ የወንጀል ህግ አንቀጽ 669(3)ለ ላይ የተመለከተውን በመተላለፍ በከባድ የስርቆት ወንጀል ጥፋተኛ ተብሎ ተቀጥቶ የነበረ በመሆኑ ልማደኛ ደጋጋሚ ልዩ የቅጣት ማክበጃ ምክንያት በመያዝ እንዲሁም አንድ ጠቅላላ የቅጣት ማክበጃ ምክንያት በመያዝ ተከሳሹን ከመሰል ድርጊት ይቆጠባል፣ ሌላውንም የማህበረሰብ ክፍል ያስተምራል ብሎ በማሰብ ጥፋተኛው እጁ ከተያዘበት ጊዜ ጀምሮ በሚታሰብ በስምንት(8) አመት ከ5 (አምስት) ወር እስራት ሊቀጣ ይገባል በማለት ውሳኔ ሰጥቷል፡፡
42 viewsAlemshet, 19:47
ओपन / कमेंट