Get Mystery Box with random crypto!

የአብክመ ፍትሕ ቢሮ ANRS JUSTICE BUREAU

टेलीग्राम चैनल का लोगो amharaattorney — የአብክመ ፍትሕ ቢሮ ANRS JUSTICE BUREAU
टेलीग्राम चैनल का लोगो amharaattorney — የአብክመ ፍትሕ ቢሮ ANRS JUSTICE BUREAU
चैनल का पता: @amharaattorney
श्रेणियाँ: राजनीति
भाषा: हिंदी
ग्राहकों: 2.34K

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


नवीनतम संदेश 60

2022-06-08 22:32:43
የምዕራብ ጎጃም ዞን ፍትህ መምሪያ የሙስና ወንጀል ጉዳዮች ክፍል ከዞኑ ፖሊስ መምሪያ የሙስና ወንጀል ጉዳዮች ክፍል ጋር በመተባበር በፍኖተ ሠላም ከተማ አስተዳደር በተመረጡ የሙስና ወንጀል ጉዳዮች ላይ ጥቆማ እንዲሠጥ ጥሪውን አቅርቧል።
48 viewsAlemshet, edited  19:32
ओपन / कमेंट
2022-06-08 22:27:42 የእንጀራ ልጁን አስገድዶ የደፈረ ተከሳሽ በ9 አመት ጽኑ እስራት ተቀጣ
ተከሳሽ ታደለ መለሰ የተባለው ግለሰብ በቀን 28/06/2014 ዓ.ም ከምሽቱ 4:00በ ሚሆንበት ጊዜ አሳቻ ጊዜን እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም የገዛ እንጀራ ልጁን አስገድዶ የደፈረ ሲሆን ጥቆማ የደረሰው ፖሊስም ምርመራ አጣርቶ በቀን 02/07/ለአየሁ ጓጉሳ ወረዳ ፍትሕ ጽ/ቤት የወንጀል ዐቃቤ ሕግ መዝገቡን መርምሮ በቀን 02/07/2014 ዓ.ም ለወረዳው ፍርድ ቤት ያቀረበ ሲሆን ፍርድ ቤቱም መዝገቡን መርምሮ በቀን 01/10/2014 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሹንም ሌሎችንም ያስተምራል ያለውን የ9 አመት ጽኑ እስራት ቅጣት አስተላልፏል በማለት የአዊ ብሔረሰብ ዞን ፍትሕ መምሪያ መረጃውን አድርሶናል፡፡
51 viewsAlemshet, edited  19:27
ओपन / कमेंट
2022-06-08 22:15:22 በቋራ ወረዳ በአልማ የሚገነቡ ት/ቤቶችን ለመገንባት ውል ወስዶ ግንባታውን በውሉ መሰረት ያላጠናቀቀው ኮንትራከተር እና አንበሳ ኢንሹራንሰ 716,567 ብር ከ40 ሳንቲም እንዲከፍሉ በፍርድ ቤት ተወሰነባቸው።

በቋራ ወረዳ መስተዳድር በአልማ አማካኝነት ከህዝብ በተሰበሰበ ሀብት በወረዳው የሚገኙ ት/ቤቶችን የማስፋፊያ ግንባታ ለመገንባት በአልማ ጉባኤ በማስወሰን ሳልፈረዲ ቁጥር 2 ት/ቤት ፣ አጋም ውሃ ት/ቤት ፣ አብተጋሆ ት/ቤት ፣ ቢኛኛ ት/ቤት እና ጉምዝ ውሃ ት/ቤትን ለማስገንባት የቋራ ወረዳ ት/ጽ/ቤት ጨረታ አውጥቶ አቶ ሙልጌታ አለነ የህንፃ ስራዎች ተቋራጭ ድርጅት ጨረታውን አሸንፎ በቀን 25/5/2012 ከተቋሙ ጋር በ 4,849,098 ብር ከ20 ሳንቲም የግንባታ ውል ወስዷል። ተቋራጩ የግንባታ ውል ሲወስድም የቅድሚያ ከፍያ ማስከበሪያ 30% እና የውል ማሰከበሪያ 10% ከአንበሳ ኢንሹራንስ ኩባንያ ዋስትና ያቀረበ ሲሆን ተቋራጩ በውሉ መሰረት ግንባታውን አጠናቆ ለቋራ ወረዳ ት/ጽ/ቤት ባለማስረከቡ ተቋሙ በተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያ በመስጠት በህግ አግባብ ውሉን አቋርጧል። የወረዳው አልማ ጽ/ቤት እና ት/ጽ/ቤት በግንባታው ላይ ሰፊ ክትትል ሲያደርግ ቆይቶ ውሉን በማቋረጥ ተቋራጩ የወሰደውን ቅድሚያ ክፍያ እንዲሁም የውል ማስከበሪያ 10% እና ሌሎች ከውሉ ጋር የሚከፈሉ ክፍያዎች በድምሩ 716,567 ብር ከ40 ሳንቲም አንበሳ ኢንሹራንሰ ጭምር ተከሶ ገንዘቡን እንዲከፍሉ እንዲደረግ ክሱን ለምዕራብ ጎንደር ዞን ፍትህ መምሪያ የቋራ ወረዳ ት/ጽ/ቤት በመላክ የህግ ድጋፍ ተደርጎለታል።

የዞን ዐቃቤ ህግም የቋራ ወረዳ ት/ጽ/ቤት የላከውን የፍትሃብሔር ክስ በመመልከት 1ኛ ተከሳሸ አቶ ሙልጌታ አለነ 2ኛ ተከሳሸ አንበሳ ኢንሹራንሰ 716,567ብር ከ40 ሳንቲም እንዲከፍሉ ለምዕራብ ጎንደር ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት አቅርቦ በመከራከር የዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት የፍትሃብሄር ችሎት በቀን 23/07/2014 ዓም በዋለው ችሎት ተከሳሾች በነጠላ እና በአንድነት 716,567. 40 ብር ለቋራ ወረዳ ት/ጽ/ቤት እንዲከፍሉ የወሰነ ሲሆን የዞን ዐቃቤ ህግም በውሳኔው መሰረት እንዲፈፀም የአፈፃፀም ክሰ በመመስረት 2ኛ ተከሳሸ አንበሳ ኢንሹራንስ በቀን 0/ 09/2014 ዓም 716,567 ብር ከ40 ሳንቲም ለቋራ ወረዳ ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ጽ/ቤት ገቢ አድርጓል።

የመንግስት የግንባታ ውሎች ፣ ፕሮጀክቶች ፣ ልዩ ልዩ ውሎች በውላቸው መሰረት እና ጥራት እንዲፈፀሙ ውል የሰጠው ተቋም በአግባቡ መከታተል ይኖርበታል።የመንግስት ሀብት ለታለመለት አላማ መዋሉን እያንዳንዱ ተቋም ክትትል ማድረግ የሚጠበቅበት ሲሆን የመንግሥት ሀብት አላግባብ ሲባክን ፣ የግንባታ ውሎች ሲጓተቱ እና ሲቋረጡ ፣ በግዝ ሒደት ብልሹ አሰራር ሲኖር በየደረጃው ያለ የመንግስት መስሪያ ቤት ክትትል በማድረግ ዐቃቤ ህግን የህግ ድጋፍ መጠየቅ የሚገባ ሲሆን መንግስት በሚከስበትም ሆነ በሚከሰስበት የፍትሃብሔር ጉዳይ በእየደረጃው ያለ ዐቃቤ ህግ እንዲከራከርበት ቀድሞ ማሳወቅ ይገባል።

መረጃው የምዕራብ ጎንደር ዞን ፍትህ መምሪያ የፍትሐብሔር የስራ ሒደት ነው።
65 viewsAlemshet, 19:15
ओपन / कमेंट
2022-06-08 15:18:21 በከባድ ስርቆት ወንጀል የተከሰሱት ተከሳሾች እያንዳንዳቸው በ4 አመት ፅኑ እስራት ተቀጡ
ተከሳሾች 1ኛ-ምናለ ብሬ
2ኛ- ጥሩአደግ አሰፍ
ተከሳሾች በ1996 ዓ.ም ተደንግጎ የወጣውን የኢፌዲሪ የወንጀል ሕግ አንቀፅ 32(1)(ሀ) እና 669(3)(ለ) የተመለከተውን ድንጋጌ በመተላለፍ ካልተያዘ ግብራበራቸው ጋር በመሆን የማይገባቸውን ብልፅግና ለራሳቸው ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት በማሰብ በቀን 25/09/2014ዓ.ም በግምት ከሌሊቱ 7:00 ሰዓት ሲሆን በሰኞ ገበያ ንዑስ/ወ/ 013 ቀበሌ ልዩ ቦታው ገደብ ተብሎ ከሚጠራው ቦታ ንብረትነቷ የሙሉጌታ በለጠ የሆነችውን አንድ ፍየል የዋጋ ግምቷ በግምት 5500(አምስት ሺ አምስት መቶ)ብር የምታወጣ ተከሳሾች ሰርቀው የወሰዱ በመሆናቸው ታስቦ በሚፈፀም የከባድ ስርቆት ወንጀል ተከሰው በማስረጃነትም ሶስት የሰው ምስክሮች እና የሰነድ ማስረጃዎች ቀርበው ተከሳሾችም በችሎት ቀርበው የእምነት ክህደት ቃላቸውን ሲጠየቁ በከፊል አምነው የዐቃቤ ሕግ ምስክሮችም በችሎት ቀርበዉ አስረድተው ተከሳሾች እንዲከላከሉ ብይን የተሰጠ ቢሆንም ተከሳሾች የመከላከያ ማስረጃ የለንም በማለታቸው በወ/መ/ስ/ስ/ህ/ቁ 149(1) መሰረት የጥፋተኝነት ፍርድ ተሰጦ በቀን 30/09/2014ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሾች የዘወትር ፀባያቸው መልካም መሆኑን እና የቤተሰብ አስተዳዳሪዎች መሆናቸውን በማገናዘብ ሁለት የቅጣት ማቅለያዎችን በመያዝ ፣ ተከሳሾችን ከእንደዚህ አይነት የወንጀል ድርጊት ያርማል ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎችን ያስተምራል ያለውን እያንዳንዳቸው ተከሳሾች በ 4 ዓመት ፅኑ እስራት የተቀጡ መሆኑን አቶ ደመቀ ጌታቸው በምስ/ጎጃ/ዞን መስተዳደር
የሰኞ/ገ/ን/ወ/ዐ/ህግ ጽ/ቤት
ተ/ኃላፊ ገልፀውልናል።
239 viewsAlemshet, 12:18
ओपन / कमेंट
2022-06-08 07:40:42
በምዕራብ ጎጃም ዞን የጃቢጠህናን ወረዳ አስተዳደር ጵ/ቤት በመተባበር በ41 ቀበሌዎች ለሚገሰሩ ለስራ እስኪያጆች ፣ ለጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች እና ለቀበሌ አስተዳዳሪዎች 19/09/2014 ዓ፡ም ወሳኝ ኩነትን አስመልክቶ ግንዛቤ ፈጠራና፣ግምገማ እና የቀጣይ አቅጣጫ ላይ ትኩረት አድርጎ መስራት እንደሚገባ መግባባት ተችሏል።የተሻለ ለሰሩ የ3 ቀበሌ ስራ አስኪያጆች የማበረታቻ ሽልማት ተሰጥቷል ።
279 viewsAlemshet, edited  04:40
ओपन / कमेंट
2022-06-07 06:50:52
358 viewsAlemshet, 03:50
ओपन / कमेंट
2022-06-07 06:50:48 በሶስተኛው ዙር የኮቪድ-19 ወረርሽኝ መከላከያ ክትባት እድሜያቸዉ ከ12 ዓመት በላይ ለሆ ኑ ከ6 ነጥብ 2 ሚሊየን በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች ለመከተብ ዝግጅት እየተደረገ ነው፡፡

የአብክመ ጤና ቢሮ የክትባት ክፍል አስተባባሪ አቶ ወርቅነህ ማሞ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንደተናገሩት የመጀመሪያ ዙር የኮቪድ-19 ክትባት በፀጥታ ችግር ምክንያት የተፈለገዉን ያክል መከተብ አለመቻሉን ገልፀዉ በሁለተኛ ዙር በተሻለ መልኩ የክትባት ዘመቻ እንደ ክልል በርካታ ጠንካራ ጎኖች የታዩበት መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ሶስተኛው ዙር የኮቪድ-19 ክትባት ደግሞ ከሰኔ 02/2014 ዓ.ም ጀምሮ እድሜያቸዉ ከ12 ዓመት በላይ ለሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች በክልላችን በሁሉም ዞኖች፣ ወረዳዎች እና ጤና ተቋማት ክትባቱ ይሰጣል፡፡

ክትባቱ ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ ስቃይና ሞት የሚከላከል በመሆኑ አብዛኛዉን የህብረተሰብ ክፍል ለመከተብ መታቀዱን ገልፀዉ ክትባቱን በተባለዉ ቀን ለመጀመር ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡

አቶ ወርቅነህ አክለዉም የኮቪድ 19 ወረርሽኝን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር በሚሰጠዉ መደበኛ ክትባት የጤና ባለሙያዎች በቡድን በመሆን ህዝብ በብዛት በሚገኝባዉ አካባዎች በትምህርት ቤቶች፣ ማረሚያዎች እና መጠለያ ካንፖች ተዘዋዉረዉ ክትባቱን ይሰጣሉ፡፡

የኮቮድ-19 ስራ የሁሉም ማበረሰብ እና ሴክተር መስሪያቤቶች ስራ በመሆኑ ለክትባቱ ስኬታማነት ርብርብ ያሰፈልጋል ብለዋል፡፡

ጤና ቢሮ
353 viewsAlemshet, 03:50
ओपन / कमेंट
2022-06-06 22:55:01 ዮ ኤስ ኤ አይ ዲ ፍትሕ ተግባራት በኢትዩጵያ ድጋፍ የአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ ያለበትን ሁኔታ የሚያሳይ ጥናት እና ስትራቴጅክ ዕቅድ ዝግጅት ስራ ማስጀመሪያ 'በጎግል ሚት' የመወያያ ማስተግበሪያ ዮ ኤስ ኤ አይ ዲ ፍትሕ ተግባራት ከፍተኛ ኃላፊዎች፣ አማካሪዎች፣ የፍትሕ ቢሮ ኃላፊዎችና ዳይሬክተሮች በተገኙበት ውይይት ተካሄደ። (ግንቦት 29 ቀን 2014ዓ.ም) በጥናቱ የቢሮው ስትራቴጂክ ዕቅድ ዝግጅት መነሻ ጥናት የሚካሄድ ሲሆን የሁኔታ ትንተና በማካሄድ ችግሮችን በመለየት ወደ ስራ ይገባል። ፍትሕ ቢሮ ካለው ኃላፊነት አኳያ ትንታኔ ይሰራል፣ኃላፊነቱን በማስፈፀም ያለበት ሁኔታ፣የውጪን የአጋር አካላት ሁኔታ፣ተቋሙ ያለበትን ደረጃ ሁኔታ ይመለከታል።ጥናቱ እና ስትራቴጂክ ዕቅዱ ሲዘጋጅ የቢሮ ማኔጅመንት አባላት እና የዞን ፍትሕ መምሪያዎች በሚያሳትፍ መንገድ እንደሚከናወን በውይይቱ ተነስቷል። አማካሪዎች የተለያዮ መረጃዎችን ለስራቸው መጠቀም ሲፈልጉ በክልል ፍትሕ ቢሮ ሆነ በተዋረድ በሚገኙ የፍትሕ መምሪያዎች በፍጥነት መረጃዎችን በመስጠት ስራው በተቀመጠለት ጊዜ እንዲከናወን ሊያደርጉ እንደሚገባ በውይይቱ ተነስቷል። ለጥናቱ እና ለስትራቴጂክ ዕቅዱ ስራ አራት አማካሪዎች በሙያቸው በትምህርት ዝግጅታቸው በተግባር አፈፃፀማቸው የተሻለ አፈፃፀም ያላቸው ተመርጠው ወደ ስራ የገቡ ሲሆን በጥናት የሚለዮ ጉዳዮችን መለየት፣የአምስት አመት ስትራቴጂክ ዕቅድ ፣የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድ ሳይንሳዊ በሆነ አሳታፊ መንገድ በተቀመጠው ጊዜ ገደብ በእንግሊዘኛና በአማርኛ ቋንቋ አዘጋጅተው ያቀርባሉ።
347 viewsAlemshet, edited  19:55
ओपन / कमेंट
2022-06-06 22:54:46
328 viewsAlemshet, 19:54
ओपन / कमेंट
2022-06-05 20:50:48 ዮ ኤስ ኤ አይ ዲ ፍትሕ ተግባራት በኢትዮጵያ የገንዘብ ድጋፍ ከአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ ጋር በመተባበር በ"ፍትሕ" የቴሌቭዥን ኘሮግራማችን "የልማት ተነሽዎች የካሣ አከፋፈል ሕጉ ምን ይላል?" በሚል ርዕስ የአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ የክልል ዐቃቤ ሕግ የሆኑት አቶ መሉጌታ አሻግሬ በአሚኮ ቴሌቪዥን የሰጡት ማብራሪያ።

125 viewsAlemshet, 17:50
ओपन / कमेंट