Get Mystery Box with random crypto!

የአብክመ ፍትሕ ቢሮ ANRS JUSTICE BUREAU

टेलीग्राम चैनल का लोगो amharaattorney — የአብክመ ፍትሕ ቢሮ ANRS JUSTICE BUREAU
टेलीग्राम चैनल का लोगो amharaattorney — የአብክመ ፍትሕ ቢሮ ANRS JUSTICE BUREAU
चैनल का पता: @amharaattorney
श्रेणियाँ: राजनीति
भाषा: हिंदी
ग्राहकों: 2.34K

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


नवीनतम संदेश 63

2022-05-26 11:06:11
177 viewsAlemshet, 08:06
ओपन / कमेंट
2022-05-26 10:48:10 በአማራ ክልል የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ለኅብረተሰቡ ተገቢውን አገልግሎት እንዲሰጡ የሚያስችል የንቅናቄ መድረክ በባሕር ዳር እየተካሄደ ነው፡፡

የአማራ ክልል ሲቪል ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ኮሚሽን በክልሉ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ለሕዝቡ ቀልጣፋና የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ በባሕር ዳር የንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።

የንቅናቄ መድረኩ ዓላማ የመንግሥት የሥራ ኀላፊዎችና ሠራተኞችን በማነቃቃት ኅብረተሰቡ ተገቢውን አገልግሎት እንዲያገኝ ማስቻል ነው።

በንቅናቄ መድረኩ ላይ የተገኙት የአማራ ክልል ምክትል ርእሰ መሥተዳድር ጌታቸው ጀምበር (ዶ.ር) በክልሉ አስተማማኝ ሰላም እንዲሰፍን ተግቶ መሥራት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል። በአሸባሪው የትግራይ ወራሪ ቡድን ምክንያት፣ በርካታ ወገኖች ሕይወታቸውን ማጣታቸውንና መፈናቀላቸውን ጠቁመዋል።

በሽብር ቡድኑ ምክንያት የተለያዩ መሰረተ ልማቶች በመዘረፋቸውና በመውደማቸው የመንግሥት አገልግሎት ተስተጓጉሎ መቆየቱን ምክትል ርዕሰ መሥተዳድሩ አስታውሰዋል። ይሁን እንጂ በኅብረተሰቡና በጸጥታ አካላት ርብርብ የተወረሩ አካባቢዎች ነፃ በመውጣታቸው የመንግሥት አገልግሎት ተመልሶ ሥራ መጀመሩን ጠቁመዋል።

የአማራ ክልል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ባንቺአምላክ ገብረማርያም ባቀረቡት የመነሻ ጽሑፍ በአማራ ክልል 417 ሺህ በላይ የሲቪል ሰርቪስ ሠራተኞች እንደሚገኙና በሚፈለገው መሰረት አገልግሎት እየሰጡ አለመሆኑን አመላክተዋል።
አብዛኛኞቹ ተቋማት ብልሹ አሠራር እንደሚታይባቸው ነው የጠቆሙት። የሄም ኅብረተሰቡ በመንግሥት ላይ እምነት እንዲያጣ እያደረገው ነውም ብለዋል።

ወይዘሮ ባንቺአምላክ እንዳሉት በየደረጃው የሚገኙ የመንግሥት የሥራ ኀላፊዎች ባለሙያው በአግባቡ ሥራውን እንዲያከናውን መደገፍ፣ ማበረታታትና መገምገም ይጠበቅባቸዋል።

በርካታ ባለሙያዎች ሥራቸው በአግባቡ ሳይመዘን አላስፈላጊ የውጤት ተኮር እንደሚሞላላቸው ኮሚሽነሯ አስረድተዋል። ስለሆነም እነዚህ ተቋማት ከግዴለሽ አሠራር ሊወጡ እንደሚገባ ነው ያስገነዘቡት። ተቋማት በስታንዳርድ የተቀመጠውን ተግባር መፈጸም እንዳለባቸውም ወይዘሮ ባንቺአምላክ ገልጸዋል።

የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ሠራተኞቻቸው የመንግሥትን የሥራ ሰዓት እንዲያከብሩ፣ መብትና ግዴታቸውን እንዲያውቁና እንዲፈጽሙ ቁጥጥር እንዲያደርጉ ጠይቀዋል። ለክልሉ እድገት አመራሩና ባለሙያው ተግባብቶና ተደጋግፎ መሥራት እንዳለባቸው ኮሚሽነሯ ገልጸዋል።

በክልሉ ለሕዝቡ ቀልጣፋ አገልግሎትን ለመስጠት:-
የሥራ ባሕልን መቀየር
የጊዜ አጠቃቀምን ማሻሻል
ምርትና ምርታማነትን መጨመር
ባለሙያውና የሥራ ኀላፊዎች ችግርን በመቋቋምና ተናብቦ ኅብረተሰቡን ማገልገል
ተጠያቂነትን መዘርጋት
ማበረታቻን መስጠት
ብልሹ አሠራርን መታገልና ማስወገድ
ከኅብረተሰቡ የሚነሱ የመልካም አሥተዳደር ጥያቄዎችን መፍታት ተጠቃሽ መፍትሔ እንደሆነ በንቅናቄ መድረኩ ተነስቷል።

ሠራተኛውንና የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችን ለማትጋት ያለመ የንቅናቄ መድረክ በክልሉ በየደረጃው የሚካሄድ እንደሆነም ተመላክቷል። አሚኮ
189 viewsAlemshet, 07:48
ओपन / कमेंट
2022-05-26 10:47:58
185 viewsAlemshet, 07:47
ओपन / कमेंट
2022-05-24 19:56:00
የአማራ ክልል ፍትህ ቢሮ ዐቃቤያነ ህግና የአስተዳደር ሠራተኞች በሕግ ማስከበር ስራዎች ዙሪያ ውይይት አደረጉ።
ለውይይት መነሻ የሚሆን መግቢያ፣የመነሻ ሁኔታዎች፣ወሳኝየስትራቴጅክ አቅጣጫ እንዲሁም የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች የሚሉ ሰፋና ዘርዘር ያሉ ሀሳቦችን የያዘ ሰነድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
ሕግየማስከበር ስራ ለፍትህ ቢሮ የዕለት ተዕለት ተግባር በመሆኑ በበጀት ዓመቱ 6 ወራት የስራ አፈፃፀም ላይ የነበሩ ክፍተቶችን ገምግሞ እና የመፍትሄ ሀሳቦችን አስቀምጦ እንዲሁም መልካም አጋጣሚዎችን ተጠቅሞ የሕግ ማስከበር ስራዎችን እየሰራ መሆኑ፤በተጨማሪም የ90 ቀናት ዕቅድ በማቀድና ውይይት በማድረግ በክልሉ የሕግ የበላይነት እንዲረጋገጥ በአዋጅ የተሰጠውን ኃላፊነቱን አየተወጣ ይገኛል።
ሕገ-ወጥ ድርጊት ፈጻሚዎች ላይ ሕግን መሰረት ያደረገ እርምጃ በመውሰድ
የሕግ ማስከበር ስራውን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባም ስምምነት ላይ ተደርሷል።
229 viewsAlemshet, edited  16:56
ओपन / कमेंट
2022-05-24 18:34:19
የአብክመ ፍትሕ ቢሮ ዐቃቤያነ ሕግና የአስተዳደር ሠራተኞች በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ በክልል ደረጃ በተዘጋጀው ሠነድ ላይ ዛሬ ግንቦት 16/2014 ዓ.ም ሰፊ ውይይት አደረጉ። የመወያያ ፅሁፉ በቢሮው ምክትል ኃላፊ ዶ/ር አያሌው አባተ አማካኝነት እየቀረበ ሲሆን ከገለፃው በኋላ ዐቃቤያነ ሕግና የአስተዳደር ሠራተኞች የተለያዮ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ያቀረቡ ሲሆን መድረኩን ሲመሩ በነበሩት የአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ ኃላፊ አቶ ገረመው ገብረጻድቅ እና የመወያያ ፅሁፍ ባቀረቡት ዶ/ር አያሌው አባተ በተነሱ ጥያቄዎች ላይ ዝርዝር ምላሽ በመስጠት መድረኩ ተጠናቋል።
248 viewsAlemshet, edited  15:34
ओपन / कमेंट
2022-05-20 22:03:12
በአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ የክልል ዐቃቤ ሕግ የሆኑት አቶ መሀመድ አብዱ ሐሠን አሜሪካን አገር ዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው አለማቀፍ የምርምር ፅሁፎችን በመፅሔት መልክ በሚያሳትመው International Journal Of Acadamic Multidisciplinary Research(IJAMR) የአካዳሚ መፅሔት አራት የጥናት የምርምር ፅሁፎችን አሳትመው አውጥተዋል።የእውቅና የምስክር ወረቀትም ተበርክቶላቸዋል። የታተሙላቸው ርዕሰ ጉዳዮች - The Common Contents Of International Investement Agreements. -The Relevancy Of Solitary Confinment in the Current Criminal Justice System. -The African Continental Free Trade Area Agreement Oppotunities and Challenges Awaiting Ethiopia. -International Environmental Law Principles An Accesment Of Ethiopia Legal and Policy framework. ናቸው። አቶ መሀመድ አብዱ ሐሠን እንኳን ደስ አለዎ! ይህ በትጋትዎ የማንበብ የመፃፍ የመተንተን ጥምር የጥረትዎ ውጤት ስለሆነ በተዋረድ የምንገኝ ዐቃቤያነ ሕግ ከአቶ መሀመድ አብዱ ሐሰን ልምድ ልንወስድ ይገባል።
256 viewsAlemshet, edited  19:03
ओपन / कमेंट
2022-05-20 10:22:01
የአማራ ክልል ሥነ-ምግባር ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ከአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ ጋራ በመተባበር ''በሙስና ወንጀሎች ማስረጃ ምዘና፣ክስ ዝግጅት እና የክርክር አመራር ክህሎት''ትኩረት ያደረገ ለሶስት ቀናት የሚቆይ ስልጠና ዛሬ ግንቦት 12 ቀን 2014ዓ.ም በእንጅባራ መሰጠት ጀምሯል። ስልጠናውን የአማራ ክልል ሥነ-ምግባርና ፀረ -ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ሀብታሙ ሞገስ እና የአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ዝጋለ ገበየሁ ስለ ስልጠናው አስፈላጊነት መልዕክት አስተላልፈው የአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ የክልል የሙስና ወንጀል ዐቃቤ ሕግ በሆኑት አቶ ግርማው አንዷለም የመወያያ ፅሁፍ እያቀረቡ ይገኛሉ።
337 viewsAlemshet, edited  07:22
ओपन / कमेंट
2022-05-19 19:33:44 በአማራ የክልል ፍትሕ ቢሮ የፍታብሔር ዐቃቤ ሕግ በሆኑት አቶ አረጋ የእኔአለም በፍትሕ ኘሮግራማችን "በነፃ የሕግ ድጋፍ አገልግሎት " በመደበኛው አማራ ሬዲዮ እና በኤፍ ኤም ጣቢያዎች የቀረበ ማብራሪያ።

344 viewsAlemshet, 16:33
ओपन / कमेंट
2022-05-19 18:13:09
በሰሜን ሸዋ ዞን የበረኸት ወረዳ ፍትሕ ጽ/ቤት በወረዳው በሚገኙ የሁሉም ቀበሌ ማህበራዊ ፍ/ቤት ዳኞችን ክህሎት ለማሳደግ ስልጠና ሰጠ፡፡
በአብክመ የማህበራዊ ፍርድ ቤት ማቋቋሚያ አዋጅ ቀጥር 246/2009 ላይ በተጠቀሱት የፍታሐብሄር ጉዳዮች ማለትም የቀበሌ ማህበራዊ ፍርድ ቤቶች በፍታብሔር ጉዳዮች አከራክሮ የመወሰን ስልጣናቸው እስከምን ድረስ ነው የሚለውን፣ ክስ መስማት ፣መጥሪያ አላላክ፣ፍርድ አሰጣጥ፣ እግድ እንዲሁም አፈፃፀምና ውሳኔ ላይ በተመለከተ እና በወንጀል ጉዳዮች ደንብ መተላለፍ የመሳሰሉትን እንዲሁም ማህበራዊ ፍርድ ቤት ለተለያዩ አካላት በሚሰጡት የማስረጃ አይነቶችን ጨምሮ ለ46 ወንድ ዳኞች እና 7 ሴት ዳኞች በድምሩ ለ53 የቀበሌ ማህበራዊ ፍርድ ቤት ዳኞች ስልጠናው በቀን 10.09.2014ዓ.ም በተሳካ ሁኔታ የተሰጠ ሲሆን ስልጠናው የተሰጠውም ከበረኸት ወረዳ አስተዳደር ጽ/ቤት ጋር በጋራ በመሆን ሲሆን የበረኸት ወረዳ ፍትሕ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኤፍሬም አዳነ ስልጠናው በየአመቱ ቀጣይነት ያለው መሆኑን ገልፀው ለዚህም የወረዳው አስተዳደር ጽ/ቤት የሚያደርገው የበጀት ድጋፍ ቀጣይነት እንዲኖረው አሳስበዋል በማለት መረጃውን ያደረሱን የወረዳ ዐቃቤ ሕግ አቶ ኤርሚያስ አስታጥቄ ናቸው፡፡
347 viewsAlemshet, edited  15:13
ओपन / कमेंट
2022-05-19 18:04:01 በ"ፍትሕ" ኘሮግራማችን ግንቦት 14 ቀን 2014ዓ.ም እሁድ ከምሽቱ 2:30፣በድጋሜ ሐሙስ ከረፋዱ 5:30 በአሚኮ ቴሌቪዥን ይጠብቁን።

332 viewsAlemshet, 15:04
ओपन / कमेंट