Get Mystery Box with random crypto!

የአብክመ ፍትሕ ቢሮ ANRS JUSTICE BUREAU

टेलीग्राम चैनल का लोगो amharaattorney — የአብክመ ፍትሕ ቢሮ ANRS JUSTICE BUREAU
टेलीग्राम चैनल का लोगो amharaattorney — የአብክመ ፍትሕ ቢሮ ANRS JUSTICE BUREAU
चैनल का पता: @amharaattorney
श्रेणियाँ: राजनीति
भाषा: हिंदी
ग्राहकों: 2.34K

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


नवीनतम संदेश 64

2022-05-18 11:11:52 በሰው መጥለፍ/ማገት/  መግደል ወንጀል የተከሰሰው በ25 አመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ተወሰነ
ተከሳሽ አበበ ዳኘው ታህሳስ 24.4.2013 ዓ.ም በግምት ከጠዋቱ 3:00 ሰአት ሲሆን ጭልጋ ወረዳ አይከል ከተማ ቀበሌ 02 ልዩ ቦታው ቀጠና 3 ሞላ አጃው ይላቅ የተባለ የ15 አመት ህፃን ልጅ በኃይል በጦር መሳርያ ጠልፎ ወደ ቤዛሆ መቀነት ቀበሌ ከወሰደ በኋላ በስልክ ወደ ሟች ታጋች ህፃን ቤተሰብ በመደወል ብር 100,000 ክፈሉ ካልከፈላችሁ ግን ህፃኑን እገድለዋለሁ በማለት ካነጋገራቸው በኋላ እንዲሰጠው የጠየቀው ብር አልተላከልኝም በሚል ህፃን ሞላ አጃው ይላቅን ገድሎ ገደል ውስጥ ጥሎት ጥር 2 ቀን 2013 ዓ.ም ተገኝቷል። የጭልጋ ወረዳ አይከል ከተማ አስተዳደር ፓሊስ ጽ/ቤት በሰው ማገት እና ሰው መግደል ወንጀል ምርመራ አጣርቶ ለማዕከላዊ ጎንደር ዞን ፍትህ መምርያ በመላክ የዞን ዐቃቤ ሕግ መዝገቡን መርምሮ የኢ ፌ ዲ ሪ የወንጀል ሕግ አንቀፅ 590/2/ሠ / እና 539/1/ሀ/ በመጥቀስ ክስ መስርቶ ለማዕከላዊ ጎንደር ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ክስ መስርቶ በማቅረብ ጉዳዩ በክርክር ቆይቶ በ1/9/2014 ዓ/ም በዋለው የወንጀል ችሎት ጥፋተኛ ተብሎ በ25 አመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ተወስናል በማለት የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ፍትሕ መምሪያ መረጃውን አድርሶናል።
220 viewsAlemshet, edited  08:11
ओपन / कमेंट
2022-05-17 22:32:37 የአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ የተለያዩ አዋጆችን፣ደንቦችን እና መመሪያዎችን ማርቀቁን ገለፀ፡፡ የሕግ ምክር ማርቀቅና ማጠቃለል ዋነኛ አላማ ሕግጋትን በማስተግበር ረገድ በሚያጋጥሙ ተግዳሮቶች ላይ ችግር ፈች ጥናቶችን በማካሄድ እና የመፍትሄ ሀሳቦችን በማፍለቅ የፍትሕ ስርዓቱ የሚሻሻልበትንና የሚጎለብትበትን ምቹ ሁኔታዎች መፍጠር ነው፡፡በክልሉ የሚወጡ ሕግጋት ለታለመላቸው አላማ እንዲውሉና የክልሉ ህዝብና መንግስት በአግባቡ ሊጠቀምባቸው የሚችሉ ሆነው እንዲረቀቁ፣ጥራታቸውን ጠብቀው እንዲዘጋጁ በማድረግ ረገድ በጊዜና በመጠን በመለካት ውጤታማ ስራ ለመስራት ጥረት ተደርጓል፡፡በመሆኑም በ2014 በጀት ዓመት 9 ወራት ውስጥ የተለያዩ 3 አዋጆች ማለትም የተሻሻለው የክልሉ አስፈጻሚ አካላት ስልጣንና ተግባራት መወሰኛ አዋጅ እና የተሻሻለው ከኃላፊነት የተነሱ የአብክመ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣የምክር ቤት አባላት፣ዳኞችና ዐቃብያነ ሕግ መብቶችና ጥቅሞች መወሰኛ አዋጅ በቡድን በአባልነት ስራዎች የተሰሩ ሲሆን የአብክመ ገቢዎች ቢሮ የኤክሳይዝ ታክስ አዋጅ ስራ ተሰርቷል፡፡ 9 ደንቦች፣19 መመሪያዎች ተዘጋጅተውና ተረቀው ለየተቋማቱ የተላኩ ሲሆን በተጨማሪም የክልሉን መንግስታዊ ተቋማት የሕግ ምክር አገልግሎት የመስጠት ኃላፊነት ለፍትሕ ቢሮ የተሰጠ በመሆኑ 11 ለሚደርሱ ጉዳዩች የሕግ ምክር አገልግሎት ተሰጥቷል፡፡
263 viewsAlemshet, 19:32
ओपन / कमेंट
2022-05-17 22:32:04 የአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ ከ132 ሚሊዬን ብር በላይ ለመንግስት ገቢ ማድረጉን ገለፀ፡፡ የአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ በ2ዐ14 በጀት ዓመት 9 ወራት የስራ አፈጻጸም በሰነዶች፣በጎ አድራጎት ድርጅቶች፣ማህበራትና ጠበቆች ጉዳይ ከክልል እስከ ታችኛው መዋቅር ድረስ ለወንድ 108 ሺህ 327፣ለሴት 50 ሺህ 288 በድምሩ ለ158 ሺህ 615 ተገልጋዮች አገልግሎት በመስጠት እና ከአገልግሎት ክፍያ 31 ሚሊዬን 050 ሺህ 390 ብር፣ከቴምብር ሽያጭ 85 ሚሊዬን 946 ሺህ 742 በድምሩ 132 ሚሊዮን 063 ሺህ 227 ብር በመሰብሰብ ወደ መንግስት ካዝና ገቢ ማድረግ ችሏል፡፡ በ9 ወራት የተስተናገዱ ተገልጋዮች እና ገቢ የሆነው የገንዘብ መጠን በ2013 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ከተስተናገደው 395 ሺህ 917 ተገልጋይ እና ተሰብስቦ ገቢ ከሆነው የአገልግሎት ክፍያና የቴምብር ሽያጭ 32 ሚሊዮን 7ዐ3 ሺህ 5ዐዐ ብር ጋር ሲነጻጸር በተገልጋይ 237 ሺህ 752 የሚያንስ ቢሆንም በገንዘብ 99 ሚሊዮን 359 ሺህ 727 ብር ብልጫ አለውደ ይህ የሆነው በሌሎች ተቋማት ይሰጡ የነበሩ የመኪናና የቤት ሽያጭ አገልግሎቶች ወደ ተቋማችን መጥተው እስከ ታችኛው መዋቅር ድረስ አገልግሎቱ እንዲሰጥ መደረጉ ተጠቃሽ ምክኒያት ነው፡፡ በተቋሙ የሚሰጡ የአገልግሎት አይነቶች ውክልና መስጠትና መሻር፣የትምህርትና ስልጠና ውል፣ትርጉም ማረጋገጥ፣የብድር ውል፣ኑዛዜ መስጠትና መሻር፣የስራ ቅጥር ውል፣የመኪናና የቤት ሽያጭ ውል፣እና ሌሎችም ውሎች ይገኙበታል፡፡
241 viewsAlemshet, edited  19:32
ओपन / कमेंट
2022-05-17 17:52:40 ከ1ሺህ በላይ የጋብቻ ጥያቄ የቀረበ መሆኑን የአማራ ክልል ፍትህ ቢሮ አስታወቀ፡፡በ2014 በጀት ዓመት 9 ወራት 1 ሺህ 219 የጋብቻ ይፈቀድልን ጥያቄ ቀርቦ ከዚህ ውስጥ 438 ቱ ለአቅመ ጋብቻ መድረሳቸው በጤና ተቋም በተደረገ ምርመራ በመረጋገጡ የተፈቀደላቸው ሲሆን 495 ቱ ደግሞ ለአቅመ ጋብቻ የደረሱ አለመሆኑን የሚገልጽ ውጤት የቀረበ በመሆኑ ጋብቻውን ቢፈፀሙ የሚደርስባቸውን መጠነ ሰፊ እና አስከፊ ጉዳት በማስረዳት በምክር እንዲቋረጥ ተደርጓል፡፡በሌላ በኩል የተሰጣቸውን ምክር ባለመቀበል እና ህግን በመተላለፍ ጋብቻ በፈጸሙ 78 ተጋቢዎች ላይ ክስ በመመስረት 9ኙን ማስቀጣት የተቻለ ሲሆን የቀሪዎቹ ጉዳይ በክርክር ሂደት ላይ ይገኛል ብለዋል፡፡የህጻናት ጋብቻ በጤና፣በስነ-ልቦና፣በኢኮኖሚ እንዲሁም በማህበራዊ ግንኙነት የሚያስከትለው ችግር ከፍተኛ በመሆኑ ሁሉም ህብረተሰብ ይህን ድርጊት የመከላከል ኃላፊነት ያለበት ሲሆን በተለይም ወላጆችና ቤተሰቦች ከፍተኛ ድርሻ ያለባቸው እና በህግም ተጠያቂ የሚያደርጋቸው መሆኑን ማስገንዘብ ይገባል፡፡ጋብቻ የሚፈጸምበት መንገድ ከጊዜ ጊዜ ስልቱን እየቀየረ እና እየረቀቀ የመጣ ከመሆኑ ጋርም ተያይዞ ፍትህ ቢሮ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ቅንጅታዊ አሰራርን የበለጠ በማሻሻልና የመግባቢያ ሰነዶችን በመፈራረም እና ያሉትንም በመከለስ ሰፊ ስራ መስራት ይኖርበታል፡፡
269 viewsAlemshet, 14:52
ओपन / कमेंट
2022-05-17 17:36:50
የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ፍትሕ መምሪያ በአዊ ብሔረሰብ አሰተዳደር ዞን በቻግኒ ከተማ አሰተዳደር የፀጥታ ጉዳዮች እና የፍትሕ ተቋማት አገልግሎት አሰጣጥን አስመልክቶ የህዝብ የምክክር መድረክ በቀን 09/09/2014 ዓ.ም የዞን እና የከተማ አሰተዳደሩ የፍትሕና ፀጥታ ተቋማት የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት ተካሂዷል።
264 viewsAlemshet, edited  14:36
ओपन / कमेंट
2022-05-17 17:34:45 የሙያ ስነ-ምግባራቸውን ባልተወጡ ጠበቆች ላይ የተለያዩ የእርምት እርምጃ መወሰዱን ፍትህ ቢሮ ገለፀ፡፡በአማራ ክልል ፍትህ ቢሮ የጠበቆች ዲሲፒሊን ጉባኤ በ2ዐ14 በጀት ዓመት 9 ወራት ውስጥ 81 ጉዳዬች ቀርበውለት የተለያዩ ውሣኔዎችን ሰጥቷል፡፡ ከተሰጡ ውሣኔዎች መካከል 15 ጠበቆች የገንዘብ መቀጮ የተቀጡ ሲሆን ከቅጣት 92 ሺህ ብር ገቢ ሆኗል፣የ1 ጠበቃ ፈቃዱ ተሰርዟል ፣የ2 ጠበቆች ፈቃዳቸው ታግዷል እንዲሁም በ3 ጠበቆች ላይ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል፡፡ጠበቆች ለፍትህ ስርዓቱ መጐልበት ያላቸው ሚና ከፍተኛ በመሆኑ የቅርብ ክትትልና እገዛ በማድረግ አቅማቸውን እንዲያጐለብቱ ማድረግ፣5ዐ ሠዓት ነጻ የህግ ድጋፍ ማድረጋቸውን መከታተል እንዲሁም የሙያ ስነ-ምግባራቸውን በማይወጡት ላይም እርምጃ መውሰድ ያስፈልጋል፡፡
247 viewsAlemshet, 14:34
ओपन / कमेंट
2022-05-17 17:29:04 ከ2 ሺህ በላይ የእጅ ከፍንጅ የወንጀል መዛግብት ውሣኔ ማግኘታቸውን የአማራ ክልል ፍትህ ቢሮ አስታወቀ፡፡በ2014 በጀት ዓመት 9 ወራት የባህርዳርና አካባቢውን ቋሚ ምድብ ጨምሮ በሁሉም የዞን ፍትህ መምሪያዎች እና በወረዳ ፍትህ ጽ/ቤቶች 916 የእጅ ከፍንጅ ወንጀል መዛግብት ቀርበው ከዚህ ውስጥ 869 መዛግብት በተፋጠነ የፍርድ አሰጣጥ ሥነ-ስርዓት ውሣኔ ያገኙ ሲሆን 47 መዛግብት በቀጠሮ ተላልፈዋል፡፡የእጅ ከፍንጅ የወንጀል ድርጊት በሚፈጸምበት ጊዜ በአፋጣኝ ክስ መስርቶ እና ማስረጃዎችንም አሟልቶ በማቅረብ በተፋጠነ የፍርድ ሥነ-ስርዓት ውሣኔ ማሰጠት እንደሚገባ የሚታወቅ ቢሆንም በ9 ወራት የቀረቡት ሁሉም መዛግብት ውሣኔ ማግኘት ሲገባቸው በቀጠሮ የተላለፋ መኖራቸው ምክንያቱ ምን እንደሆነ በመለየትና የመፍትሄ ሀሳብ በማስቀመጥ ከችግሩ መውጣት ይገባል፡፡ህብረተሰቡም የእጅ ከፍንጅ የወንጀል ድርጊቶች በተፋጠነ የፍርድ ሥነ-ስርዓት ታይተው ውሣኔ እንዲያገኙ ኃላፊነት እና ድርሻ ያለበት መሆኑን ተገንዝቦ ከፖሊስና ከዐቃቤ ህግ ጋር ተባብሮ በመስራት ለፍትህ ስርዓቱ መከበር የዜግነት ግዴታውን መወጣት ይኖርበታል፡፡
251 viewsAlemshet, 14:29
ओपन / कमेंट
2022-05-17 11:04:41 በአማራ የክልል ፍትሕ ቢሮ የፍታብሔር ዐቃቤ ሕግ በሆኑት አቶ አረጋ የእኔአለም በፍትሕ ኘሮግራማችን "በነፃ የሕግ ድጋፍ አገልግሎት " በመደበኛው አማራ ሬዲዮ እና በኤፍ ኤም ጣቢያዎች የቀረበ ማብራሪያ።
286 viewsAlemshet, edited  08:04
ओपन / कमेंट
2022-05-17 10:58:59
መሰረታዊ መብቶች አንዱ ስለሆነው በህግ ባለሙያ የመታገዝ መብት ምን ያህል ያውቃሉ ? በአማራ ራዲዮና አማራ ኤፍ ኤም ባ/ዳር 96.9 መሰናዶ ይከታተሉ፡፡
296 viewsAlemshet, 07:58
ओपन / कमेंट
2022-05-17 08:01:01
በ"ፍትሕ"የቴሌቪዥን ፕሮግራማችን "የቋሚ ንብረት ምዝገባ እና ስመ-ንብረት ዝወውር" በተመለከተ ሕጉ ምን ይላል? በአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ የሰነዶች የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችና የጠበቆች ጉዳይ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በሆኑት አቶ ዮሐንስ ተገኘ ማብራሪያ በቅርብ ቀን በአሚኮ ቴሌቪዥን ይቀርባል።ይጠብቁን?
75 viewsAlemshet, edited  05:01
ओपन / कमेंट