2022-06-15 04:52:24
በኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን የአርጡማ ፉርሲ ወረዳ ፍትሕ ጽ/ቤት ከUNDP በተገኘ የገንዘብና የቴክኒክ ድጋፍ "ነፃ የሕግ ድጋፍ አገልግሎት የሴቶችን መብት ለማረጋገጥ" በሚል መሪ ቃል በወረዳው ውስጥ ለሚገኙ የወረዳ ፍርድ ቤት ዳኞች፣የሴቶችና ህፃናት ኃላፊና ባለሙያ እንዲሁም የወረዳው ፖሊስ ጽ/ቤት በተገኙበት ስልጠና ሰጠ
(ሰኔ 7 ቀን2014ዓ.ም) በስልጠናና የአጋር አካላት ውይይቱ ላይም የወረዳው ም/አስተዳዳሪ ወ/ሮ ሐዋ መሐመድ የተገኙ ሲሆን የመክፈቻ ንግግር በማድረግ ፕሮግራሙን በይፋ አስጀምረዋል።
በተጨማሪም በስልጠናው ላይ ከተለያዩ ቀበሌዎች የተወጣጡ ለፆታዊ ጥቃት ተጋላጭ የሆኑ እና ጉዳያቸው እልባት ያላገኙላቸው ሴቶችና ቤተሰቦች የተገኙ ሲሆን በጉዳዩ ላይ ሰፊ ውይይት ከተካሄደ በኃላ የመፍትሔ አቅጣጫዎችም ተመላክተዋል።
በመጨረሻም በሴቶችና ህፃናት፣ በፖሊስ እና በፍትሕ ጽ/ቤቶች መካከል ሊኖር የሚገባውን የመረጃ ልውውጥ ፎርማቶች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸው በመረጃ ቅብብል ፎርማቶቹ መሰረት ተግባራትን ልንከውን እንደሚገባ ከስምምነት ላይ ተደርሷል።
332 viewsAlemshet, edited 01:52