Get Mystery Box with random crypto!

የአብክመ ፍትሕ ቢሮ ANRS JUSTICE BUREAU

टेलीग्राम चैनल का लोगो amharaattorney — የአብክመ ፍትሕ ቢሮ ANRS JUSTICE BUREAU
टेलीग्राम चैनल का लोगो amharaattorney — የአብክመ ፍትሕ ቢሮ ANRS JUSTICE BUREAU
चैनल का पता: @amharaattorney
श्रेणियाँ: राजनीति
भाषा: हिंदी
ग्राहकों: 2.34K

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


नवीनतम संदेश 11

2023-03-09 18:37:20

211 viewsAlemshet Miheretie, 15:37
ओपन / कमेंट
2023-03-09 18:21:38 የርስበርስ ግድያን የሚፀየፍ ማህበረሰብ ለመገንባት የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ሚናቸውን ሊወጡ ይገባል ተባለ

በዛሬው እለት ማለትም በ29/6/2015 ዓ/ም የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ በተገኙበት በምስራቅ ና ምዕራብ ደንቢያ፣ጎንደር ዙርያ ወረዳ ከጊዜ ወደጊዜ እየጨመረ የመጣውን የርስበርስ በርስ ግድያ ለማስቆም ያለመ የምክክር መድረክ በምእራብ ደንቢያ ወረዳ በጯሂት ከተማ ተካሂዷል።

በሦስቱ ወረዳዎች ከግድያ መስፋፋት ጋር ተያይዞ በመንስኤዎቻቸው፣ ባስከተለው ጉዳት እና በመፍትሔዎቻቸው ዙሪያ ጥናት የተካሔደ ሲሆን፦ በተካሄደው ጥናትም የስራ ሃላፊዎች፣ የሀይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የፍትህ እና የፀጥታ አካላት በተገኙበት የጥቁር ደም መባቃቀልን ማስቆም የሚያስችል ጥናት በምእራብ ደንቢያ ወረዳ ፍትህ ጽ/በት አቅራቢነት ምክክር አካሂደዋል።

በጥናቱ ለርስበርስ ግድያ መስፋፋት ዋናው ምክንያት የጦር መሳሪያ መብዛት ና የአያያዝ ችግር ፣ መሬት፣ የሀሰት ምስክር፣ ደም ምለሳ፣ የስራ አጥነት ፣የገጠር አረቂ ቤቶች  መስፋፋት፣ሕገወጥ የጥይት ተኩስ፣ ስርቆት ና ወንጀል ፈፃሚዎች ላይ አስተማሪ ቅጣት አለመስጠት ከተጠቀሱት ዋና ዋና ችግሮች ጥቂቶቹ ናቸው ።

በዚህም የተነሳ በነዋሪዎች ላይ መፈናቀል ይደርሳል፣መሬት ሳይዘራ ይቀራል ብዙዎቹ ለረሀብ እና እንግልት ይጋለጣሉ፣ ስነ-ልቦናዊ ጉዳት ይደርስባቸዋል ፣ የንብረት ዘረፋና ልጆች ከትምህርት ገበታቸው እንዲፈናቀሉ ያደርጋል።

ይህን የርስ በርስ ግድያ ችግር ለማስቆም በመፍትሔነት የተጠቀሱት ደም አድርቅ የሀገር ሽማግሌዎችን ማቋቋም፣ አገር በቀል የሰላም እና የልማት ሲቪክ ማህበራትን ማቋቋም ሕገወጥ የጥይት ተኩስን ማስቆም ፣የጦር መሳርያ አያያዝን እና ሕጋዊነቱን መቆጣጠር፣የፍትህ አካላት ቅንጅታዊ አሰራርን ማጠናከር ፣አስተማሪ ውሳኔዎችን ማሰጠት፣ የሀይማኖት አባቶች ተከታዮቻቸውን ሃይማኖታዊ አስተምህሮዎችን ሊወጡ እንደሚገባ በምክክር መድረኩ ተገልጿል።
የህገወጥ የጦር መሳሪያ አያያዝ መበራከት የሚታዩ የአፈፃፀም ችግሮችን  ቁጥጥር እና ክትትል በማድረግ የፀጥታ አካላት ሕገወጥ የጥይት ተኩስን ከማስቆም ይልቅ አልፍ አልፍ የወንጀለኛ ተባባሪ መሆን በሚመለከት  መንግስት ሃላፊነቱን ወስዶ  በግልፅ የሚታዩ ችግሮችን ለመቅረፍ ከሕዝብ ጋር በመተባበር ሊሰራ እንደሚገባ ነው በመድረኩ የተገለፀው።

በአጠቃላይ የሚከሰቱ ፈተናዎችን ለመቋቋም በጋራ ውስጣዊ አንድነት ማጠናከር ላይ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ አቅጣጫ ተቀምጧል በማለት የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ፍትሕ መምሪያ ያደረሰን መረጃ ለማወቅ ተችሏል።
194 viewsAlemshet Miheretie, edited  15:21
ओपन / कमेंट
2023-03-09 18:21:24
169 viewsAlemshet Miheretie, 15:21
ओपन / कमेंट
2023-03-09 16:59:36
193 viewsAlemshet Miheretie, 13:59
ओपन / कमेंट
2023-03-09 16:59:34
185 viewsAlemshet Miheretie, 13:59
ओपन / कमेंट
2023-03-04 22:46:58 የአመራር ክህሎት እና ስትራቴጂያዊ የአስተዳደር ስልጠና ለአመራሩ መሰጠቱ የአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ ተፈጻሚነት ወሳኝ ሚና እንዳለው ተገለጸ፡፡
(የካቲት 24 ቀን 2015ዓ.ም) የተከበሩ አቶ ማንደፍሮት በላይ በዩ ኤስ ኤ አይ ዲ ፍትሕ ተግባራት በኢትዩጵያ ምክትል ኃላፊ የአመራር ክህሎት እና ስትራቴጂያዊ የአስተዳደር ስልጠና በጎንደር ከተማ ሲሰጥ በመድረኩ መክፈቻ እንደገለጹት ዩ ኤስ ኤ አይ ዲ ፍትሕ ተግባራት በኢትዩጵያ ከአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ ጋር ባለፉት ሶስት ዓመታት በትብብር ሲሰራ እንደቆየ ገልጸው ፤እስካሁን የነበረው ትብብር ውጤታማም ነበር ብለዋል፡፡ ብዙዎቻችሁ ከፕሮጀክታችን ጋር በትብብር በተዘጋጁ ወርክሾፖች ተሳታፊ እንደነበራችሁ እገምታለሁ ያሉት አቶ ማንደፍሮት በዩ ኤስ ኤ አይ ዲ ፍትሕ ተግባራት በኢትዩጵያ አንዳንድ በተመረጡ ቦታዎች ላይ በተደረገው የቴክኖሎጂ ድጋፍና አገልግሎት አሰጣጥን ለማሳለጥ የተሰሩ ስራዎችን ለማስተባበር ብዙ ስራዎች ተሰርተዋል፡፡በዩ ኤስ ኤ አይ ዲ ፍትሕ ተግባራት በኢትዩጵያ ትብብር ከጥቂት ወራት በፊት አማካሪዎችን በመመደብ የአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ አምስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ እንዲዘጋጅ ተደርጓል ብለዋል፡፡
እኒዚህን ስራዎች ወደ ታች ለማውረድ የአመራሩ ቀርጠኝነት ወሳኝ እንደነበር አስታውሰው ለዚህ ደግሞ የሚያስፈልጉ ስልጠናዎች ልምድ ባላቸው ባለሙያዎች እንዲሰጥ የአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ ለፕሮጀክታችን ባቀረበው ጥያቄ መሠረት ይሄንን የዛረውን ስልጠና ለማዘጋጀት ችለናል ብለዋል፡፡ ይሄ ስልጠና በሁለት ዙር ለአመራሮቹ ሲሰጥ የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ ተግባራዊነት ወደ ስራው ለመግባት እንደ ትጥቅ የሚቆጠር በመሆኑ ውጤታማ እንደሚሆን ተስፋ አለኝ ብለዋል፡፡
ዩ ኤስ ኤ አይ ዲ ፍትሕ ተግባራት በኢትዩጵያ አስካሁን በነበረው እንቅስቃሴ ብዙ ዙር ስልጠናዎች በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዩች ተሰጥተዋል፤የሕግ ማዕቀፎች፣ማንዋሎች እንዲዘጋጁ ድጋፍ ተደርጓል፡፡በአማራ ክልል የሕግ የበላይነት ለማስከበር በሚደረገው ጥረትም በየደረጃው ያለው ኃላፊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ያደረገው ጥረት የሚበረታታ ነው ብለዋል፡፡
ዩ ኤስ ኤ አይ ዲ ፍትሕ ተግባራት በኢትዩጵያ ፐሮጀክት ከፍትሕ ሴክተሩ ጋር ሲሰራው የቆየ ተግባራት ሐምሌ 2015ዓ.ም የሚጠናቀቅ ሲሆን፤አሁን እየተሱ ያሉት የማጠናቀቂያ ስራዎች ናቸው፡፡ወደፊት ፕሮጀክቱ በአዲስ ሲመጣ ተመሳሳይ እና የተሸለ ስራ ይሰራል፡፡ ተነሳሽነቱ ፣ግፊቱ ፣ጥያቄዎቹን ማቅብ ከእናንተ ከአመራሮቹ ሊመጣ ይገባል፡፡ፕሮጀክቶችን፣ስትራቴጂዎችን ማምጣት፣ውጤት ሊያመጡ የሚችሉ ቤዝ ላይኖችን መለየት ይገባል፡፡አመራሮች ለባለሙያዎች በማስገንዘብ እንዳንዱ በለሙያ በስትረቴጂክ ዕቅዱ ለየትኛው ዓለማ እየሰራሁ ነው ያለው ብሎ ሊያውቅና ሊተገብር ይገባል ብለዋል፡፡
85 viewsAlemshet Miheretie, edited  19:46
ओपन / कमेंट
2023-03-04 22:46:42
83 viewsAlemshet Miheretie, 19:46
ओपन / कमेंट
2023-03-04 10:10:27
የጃማ ወረዳ ፍትሕ ጽ/ቤት ዐቃቢዐነ ሕግ የሆኑት አቶ ነብዩ ጊዮንና ወ/ሮ ራሄል ዘመድኩን በወረዳው ቀበሌ 017 እና 06 ቀበሌዎች በሕገ ወጥ የመሬት ወረራ፣ በህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር፣ የጦር መሳሪያ አስተዳደርና ቁጥጥር፣ ያለ እድሜ ጋብቻ፣ አስገድዶ መድፈር፣ ጠለፋ፣ ስርቆት፣ ድብደባ፣ የሰዎች ግድያ፣ ሀሰተኛ ምስክር ዙሪያ የካቲት 21 እና 22 ቀን 2015 ዓ.ም የንቃተ ሕግ ትምህርት ለቀበሌ የማህበረሰብ ክፍሎች ሰጥተዋል።
325 viewsAlemshet Miheretie, edited  07:10
ओपन / कमेंट
2023-03-04 08:20:58 የአማራ ብሔራዊ ክልል መንግስት  ፍትሕ ቢሮ ከዩ ኤስ ኤ ይዲ ፍትሕ ተግባራት በኢትዩጵያ ጋር በመተባበር  ለተቋሙ ከፍተኛ እና መካከለኛ  ደረጃ ኃላፊዎች የአመራር  ክህሎት እና ስትራቴጂያዊ አስተዳደር ትኩረት ያደረገ ሥልጠና ከየካቲት 24 እስከ 25 ቀን 2015 ዓ.ም በጎንደር ከተማ እየተሰጠ ይገኛል፡፡
የአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ ኃላፊ ተከበሩ አቶ ገረመው ገብረጻድቅ በመክፈቻ ንግግራቸው እንደገለፁት የአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ ከዩኤስኤአይዲ ፍትሕ ተግባራት በኢትዩጵያ በጀትና የቴክኒክ ድጋፍ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠናዎችን ፣የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ እና የማንዋል ዝግጅት ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን አስታውሰው ይሄን መሠረት በማድረግ የአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ የአሰራር እና የአደረጃጀት ማንዋል በመፈተሸ ወደ ስራ በማስገባት አዳዲስ አመራሮችን ሰይመን ወደ ስራ ተገብቷል፡፡አደረጃጀትና አሰራሩ ከክልል እስከ ወረዳ የሚያካትት በመሆኑ የተሰጠው ስልጠና ፣ተዘረጉት አሰራሮች፣የተዘጋጀው ማንዋል እና የተፈጠረው አደረጃጀት እና የሰየምናቸው ኃላፊዎች የአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ አላማ ለማሳካት መነቃቃት የፈጠረ እንደሆነና ወደ ስራ ተገብቶ ለውጦችንም እያን ነው ብለዋል፡፡
ይሄ በቂ ነው ለማለት ስለማያስችል አብዛኛው የፍትሕ ሴክተር አመራር ወደ አመራርነት የሚመጣው ከባለሙያነት ተነስቶ ስለሆነ ዘመናዊ የሆነ የአመራር ብቃት ማሳደጊያ ስልጠና አስፈላጊ መሆኑ ስለታመነበት በዘመናዊ የአመራር ክህሎት እና ስትራቴጂያዊ አስተዳደር ላይ ትኩረት አድርጎ በስልጠናው ላይ የአመራር አይነቶችን በመውሰድ ተቋማችን ላይ ተግባራዊ በማድረግ ተቋማችንን መምራት ይገባል ብለዋል፡፡
የአማራ ክልል ሰፊ ህዝብ  የሚያስተዳድር ክልል  ነው፡፡በክልሉ ውስጥ የሕግ የበላይነት እንዲሰፍን፣ በየትኛውም ደረጃ በማንኛውም አይነት የሚገለጽ  ሕገ-ወጥ ተግባራት መልክ በማስያዝ የአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ ማዕከላዊ ተቋም  መሆኑን የማረጋገጥ ኃላፊነት አለበት፡፡ይሄንን ለመወጣት ሁላችንም የድርሻችንን የአመራር ሚና መወጣት አለብን ብለዋል፡፡
ዛሬ እና በቀጣይ ዙር ስልጠናውን የምትወስዱ የተቋማችን አመራሮች አመራርነት ሚናችሁ እናንተ ላይ ወደቀ በመሆኑ የአመራር ክህሎትና ስትራቴጂዊ አስተዳደር  ላይ መግባባት በመፍጠር  ከላይ ሆኖ ራስን እየተመለከቱ ፣የሕዝብን ስሜት እያዳመጡ ጥረት፣ትጋት በማሳየት በሥነ-ምግባራችን የተመሰገን መሪ ልንሆን ይገባል ብለዋል፡፡
በመጨረሻም  የምን ጊዜም ተባባሪያችን የሆነው የዩ ኤስ ኤ ይዲ ፍትሕ ተግባራት በኢትዩጵያ  የበላይ ኃላፊዎች ሚስተር ዴቪድ እና አቶ ማንደፍሮት በላይ ፕሮጀክቱ ከእኛ ጋር የሚሰራውን ስራ አጠናቆ ቢወጣም ይህ ስልጠና ቀደም ብለን የጠየቅን በመሆኑ አስፈላጊነቱን በመረዳት በጀቱን ስለፈቀዱልን በቢሮው ስም ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
355 viewsAlemshet Miheretie, edited  05:20
ओपन / कमेंट
2023-03-04 08:17:00
295 viewsAlemshet Miheretie, 05:17
ओपन / कमेंट