Get Mystery Box with random crypto!

ስለዚህ አንድ ሰው ከዋና መኖሪያ ከጠፋ ማንም ሰው የመጥፋት ውሳኔ እንዲሰጥ ለማመልከት ይችላል፡፡ | የአብክመ ፍትሕ ቢሮ ANRS JUSTICE BUREAU

ስለዚህ አንድ ሰው ከዋና መኖሪያ ከጠፋ ማንም ሰው የመጥፋት ውሳኔ እንዲሰጥ ለማመልከት ይችላል፡፡ የመጥፋት ውሳኔን ለመስጠት ዳኞች ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለባቸው ከህጉ የምንረዳው ነው፡፡ ለዚህም የሰውየውን መጥፋት ለመረዳት ዳኞች ከዓቃቤ ህግ ጋር በመተባበር በማናቸውም ቦታ ይልቁንም የጠፋው ሰው የመጨረሻ ይኖርበት ከነበረው ቦታ እና በመጨረሻ መኖሩ የታየበት ቦታ ጠፋ የሚባለው ሰው ስለመኖሩ ምርመራ እንዲደረግ በማዘዝ እንደሆነ የፍትሐብሄር ህግ አንቀፅ 156 ስር ተደንግጓ እናገኘዋለን፡፡ ይኸውም ዓቃቤ ህግ ስለመጥፋቱ የቀረበውን ማመልከቻ እና ማስረጃዎች ፍርድ ቤቱ ወደ ትክክለኛ ውሳኔ ለመድረስ የሚያስችለውን ማስረጃ ዓቃቤ ህጉን ተቃርኖ የበለጠ እንዲረጋገጥ በማድረግ ነው፡፡ ስለዚህ ዳኞች የጠፋው ሰው አጠፋፍ ‹መሞት የሚመስል› መሆኑን የማረጋገጥ ግዴታ ይጣልባቸዋል፡፡ መጥፋቱን ከተረዱት በፍትሐብሔር ህግ አንቀፅ 157 መሰረት የመጥፋት ውሳኔ የመጨረሻ ወሬዎቹን የተሰማበትን ቀን በመጥቀስ ውሳኔ ይሰጣሉ፡፡ በሌላ በኩል ዳኞቹ ያገኙት ማስረጃ ወደሞት የሚያመዝን መስሎ ከታያቸው ‹የሞት ማስታወቂያ› ፍርድ ይሠጣሉ ሲል የፍትሐብሔር ህግ አንቀፅ 157(1) ደንግጓል፡፡ ዳኞች እንደነገሩ ሁኔታ የመጥፋት ውሳኔውን ወይም የመጥፋት ውሳኔ ማስታወቂያን ለአንድ አመት መቅጠር የሚችሉ ሲሆን ነገር ግን የመጥፋት ውሳኔው ከተጠየቀ ከአንድ አመት በኋላ ወይም ሰውየው ከጠፋ አምስት አመት በኋላ የመጥፋት ውሳኔ መሰጠት አለበት፡፡