Get Mystery Box with random crypto!

#በአልጣሽ ብሔራዊ ፓርክ ላይ በደን አዋጅ የተከለከለ ተግባር የፈፀ ተከሳሽ በእስራት እና በገንዘብ | የአብክመ ፍትሕ ቢሮ ANRS JUSTICE BUREAU

#በአልጣሽ ብሔራዊ ፓርክ ላይ በደን አዋጅ የተከለከለ ተግባር የፈፀ ተከሳሽ በእስራት እና በገንዘብ ተቀጣ
******
ከሳሽ፦ዐ/ህግተከሳሽ፦አብዱ ተበጀ አድራሻ ቋራ ወረዳ መሀዲድ ቀበሌ ተከሳሽ የኢፌድሪ የወንጀል ህግ አንቀፅ 32(1)(ሀ)እና 1ኛ.የደን ልማት ጥበቃ እና አጠቃቀም አዋጅ ቁጥር 1065/2010 አንቀፅ 25(4)(ረ)እና አንቀፅ 26(1)ን እና 2ኛ.የደን ልማት ጥበቃ እና አጠቃቀም አዋጅ ቁጥር 1065/2010 አንቀፅ 25(4)(ሀ) እና አንቀፅ 26(8)ን በመተላለፍ በፈፀማቸዉ ሁለት ወንጀሎች ተከሷል።

ተከሳሽ ሌሎች ካልተያዙ ግብረ አበሮች ጋር በመሆን መጋቢት 7/2015 ዓ/ም በግምት ከጥዋቱ 3:00 ሳአት ቋራ ወረዳ መሀዲድ ቀበሌ ከአልጣሽ ብሔራዊ ፓርክ ዉስጥ ልዩ ቦታዉ ስሁል እየተባለ ከሚጠራዉ በህገወጥ መንገድ በመግባት ከፓርኩ ዉስጥ በግምት 20 ኪሎ ግራም ማር እና 82 የወንበላ ዛፍ የቆረጠ በመሆኑ በፈፀመዉ በደን አዋጅ የተከለከለ ተግባር በሁለት ወንጀሎች ተከሷል።

ተከሳሽም ድርጊቱን መፈፀሙን ያመነ እና የቀረበበትን ክስ ያልተቃወመ በመሆኑ ጥፋተኛ ተብሏን።

ፍ/ቤቱም ዐ/ህግ ያቀረበዉን ክስ በመመርመር እና ተከሳሽም ድርጊቱን መፈፀሙን ያመነ በመሆኑ 4(አራት) የቅጣት ማቅለያዎችን እና 1(አንድ) የቅጣት ማክበጃን በመያዝ በቀን 19/07/12015ዓ/ም በዋለው የወንጀል ችሎት ተከሳሽን ያርማል መሰል ድርጊት ፈፃሚዎችን ያስተምራል ብሎ ያመነበትን በተሰጠዉ ፍቅድ ስልጣን በ5 (አምስት)አመት ፅኑ እስራት እና በ1,500 (አንድ ሺ አምስት መቶ)ብር ይቀጣ ሲል ዉሳኔ ሰጥቷል።

/ቋራ ወረዳ ፍ/ቤት/